www.maledatimes.com የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግማሽ ቢሊዮን ብር የሚጠጋ በጀት ሥራ ላይ አልዋለም - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግማሽ ቢሊዮን ብር የሚጠጋ በጀት ሥራ ላይ አልዋለም

By   /   March 31, 2019  /   Comments Off on የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግማሽ ቢሊዮን ብር የሚጠጋ በጀት ሥራ ላይ አልዋለም

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 24 Second

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በየበጀት ርዕሱ በመደበኛ በጀት 10 በመቶ ብቻ በመውሰድ 444 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በሥራ ላይ እንዳላዋለ ታወቀ።

የሚንስቴሩ የ2009 የሒሳብ ኦዲት ግኝት በመንግሥት ወጪ ቁጥጥር ጉዳዮች አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ በተገመገመበት ወቅት እንደተገለፀው፣ በሥራ ላይ ያልዋለው በጀት ከአጠቃላይ በጀቱ ጋር ሲነፃፀር 20 በመቶ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በ2009 በሌላ የበጀት ርዕስ ላይ ከተቀመጠው በጀት 330 ሚሊዮን ብር እላፊ መጠቀሙንም የሚያሳይ ኦዲት ግኝት እንደታየበት ተገልጿል።

ከዚህም በመነሳት በኢትዮጵያ ውስጥ ለቁጥር የሚያዳግቱ የመንግሥት ፕሮጀክቶች በበጀት እጥረት ምክንያት እየተዘጉ ባለበት ሁኔታ ከመደበው በጀት ጥቂት ሊባል የሚችል የበጀት አጠቃቀም እንዴት በሚንስቴሩ ላይ ሊታይ እንደቻለ በቋሚ ኮሚቴው ተጠይቆ፤ ሚንስቴሩ በጀትን በዕቅድ ከመምራት አንፃር ያለበትን ሁኔታ ማብራሪያ እንዲሰጥ ታዟል።

ለቀረበው ጥያቄ ምለሽ ለመስጠት ውጭ ጉዳይ ሚንስቴርን ወክለው የተገኙት በሚንስትር ዲኤታ ማዕረግ የሰው ኃብትና ፋይናንስ ዳይሬክተር አምባሳደር ብርቱካን አያሌው በሚንስቴሩ መረጃ መሰረት የበጀት አጠቃቀሙ 92 በመቶ እንደሆነና ተራፊ በጀት ከመጠን በላይ እንዳይሆንም ከፍተኛ ቁጥጥር መሥሪያ ቤቱ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።

በዚህም ምክንያት ዋና መሥሪያ ቤቱ ሥር ባሉ በመላው ዓለም የተሰራጩ 46 ሚሲዮኖችና 14 ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች ወጯቸው የበጀት ዓመቱ ሳያልቅ በየመሐሉ ቁጥጥር እንደሚደረግም ነው ያስረዱት። አያይዘውም ሚንስቴሩ የሚያሳየው ቁጥጥር በፌደራል ዋና ኦዲተርም ምስጋና እንደተቸረው ተናግረዋል።

ከሚንስቴሩ የተሰጠውን ምላሽ ተከትሎ የፌደራል ዋና ኦዲተር ገመቹ ዱቢሶ ˝መሥሪያ ቤቱ ራሱን እንዳያታልል˝ ሲሉ መክረዋል። ˝ይህን ያህል የበጀት አጠቃቀም ጉድለት እያለባችሁ በፌደራል ኦዲተር ምስጋና ተችሮናል ማለት የማይመስል ነገር ነው˝ ብለዋል። አሁንም ቢሆን ሚንስቴሩ ከፍተኛ የበጀት አጠቃቀም ጉድለትና የኦዲት ግኝት ያለበት በመሆኑ ትልቅ ሥራ እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል። እየታየ ያለው የበጀት አጠቃቀም ጉድለት በወንጀል የሚያስከስስ ነው ሲሉም አስጠንቅቀዋል።

ሚንስቴሩ ከተሰብሳቢ ሒሳብ ጋር በተገናኘ የኦዲት ክፍተቶች እንዳሉበት ከቋሚ ኮሚቴው የተነሳ ሲሆን፤ ተወራርዷል ከተባለው 43 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ውስጥ 7 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብሩ ማስረጃ እንደሌለው ተገልጿል። በመጨረሻም ዋና ኦዲተሩ መረጃ ሳይኖራቸው እንደተወራረዱ የሚቆጠሩት ሒሳቦች መረጃ እስካልቀረበባቸው ድረስ ተመልሰው እንዲተከሉ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on March 31, 2019
  • By:
  • Last Modified: March 31, 2019 @ 1:20 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar