www.maledatimes.com ሕገ ወጥ ኤጀንሲዎች በርካታ ሴቶችን ለዝሙት አዳሪነት እየተጠቀሙባቸው መሆኑ ተገለጸ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ሕገ ወጥ ኤጀንሲዎች በርካታ ሴቶችን ለዝሙት አዳሪነት እየተጠቀሙባቸው መሆኑ ተገለጸ

By   /   March 31, 2019  /   Comments Off on ሕገ ወጥ ኤጀንሲዎች በርካታ ሴቶችን ለዝሙት አዳሪነት እየተጠቀሙባቸው መሆኑ ተገለጸ

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 16 Second

ሕገ ወጥ አሰሪና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች በመርካቶ አካባቢ ምንም ፈቃድ ሳይኖራቸው፣ በርካታ ሴቶችን ወደ ውጭ አገር እንወስዳችኋለን በሚል ሰበብ በአንድ ቤት ውስጥ በማከማቸት ለዝሙት አዳሪነት ጭምር እየተጠቀሙባቸው መሆኑን አዲስ ማለዳ አረጋገጠች።

በጉዳዩ ዙሪያ አዲስ ማለዳ ያነጋገረቻቸው የአዲስ አበባ አስተዳደር የሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አስፋው መብራቴ፣ በመርካቶ አካባቢ እንደዚህ ዓይነት ወንጀሎች እንደሚፈጸሙ መረጃዎች እንዳላቸውና ከአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ስብሰባም ነዋሪው ይህንን እንዳረጋገጠላቸው አምነው፣ እንዲህ ዓይነቱን ወንጀል ለማስቀረት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰሩ መሆኑንና እስካሁን ባለው ደረጃ ፍቃድ ሳይኖራቸው የሚሰሩ 1034 ኤጀንሲዎችን በመዝጋት ዘመቻ መጀመራቸውን ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ አስተዳደር የሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ቢሮ በከተማዋ የሚገኙ ከአንድ ሺሕ የሚበልጡ ሕገወጥ አሠሪ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎችን ማገዱን ለአዲስ ማለዳ የተናገሩት አስፋው፣ በአዲስ አበባ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲነት ሲሰሩ መቆየታቸውንና ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጣ ግብረ ኀይል ባደረገው የተደራጀ ቁጥጥር አብዛኛው የዘርፉ ሥራ ለሕገ ወጥነት ተጋላጭ ሆኖ መቆየቱን አስታውቀዋል። በተመሳሳይ 20 መሰል ተቋማት ሐሰተኛ ማስታወቂያዎችን በመለጠፍ ሕዝብ ሲያምታቱና ሲያጭበረብሩ መቆየታቸውን የቢሮው ምክትል ኃላፊ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

ፍቃድ ባወጡበት ቦታ አለመገኘት፣ አላግባብ ገንዘብ መቀበል፣ ሕጋዊውን የፈቃዱን መስፈርት ሳያሟሉ በሥራ ላይ መገኘት ኤጀንሲዎቹ የተገኘባቸው ችግር ሲሆን፣ አብዛኞቹም እየታሸጉ ነው ተብሏል። ለተቀጣሪ ሠራተኞች ስለ ክፍያና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ግልጽ የሆነ መረጃ አለመስጠትም ለውዝግብ ምንጭ መሆኑን ቢሮው አደረግኩት ባለው ማጣራት እንደደረሰበት ያስታወቀ ሲሆን፣ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና ሕዝቡም ሕጋዊ የሆኑትን ለይቶ እንዲጠቀም እና በሕገወጦች ላይ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበርም ጥሪ ቀርቧል።

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መርካቶ ፖሊስ ጣቢያ መርማሪ የሆኑት ኮማንደር ኤርሚያስ፣ እንደዚህ ዓይነት የወንጀል መዝገቦች እጃቸው ላይ መኖሩን ለአዲስ ማለዳ ገልጸው፣ ጉዳዩ በምርመራ ላይ በመሆኑ መረጃ ለመስጠት ያስቸግራል፤ ምርመራውን ጨርሰን ክስ ስንመሰርት የምናሳውቃችሁ ይሆናል ብለዋል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on March 31, 2019
  • By:
  • Last Modified: March 31, 2019 @ 1:27 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar