www.maledatimes.com ወደ ቀያቸው የተመለሱ የቤኒሻንጉል ተፈናቃዮች እርዳታ ተቋርጦብናል አሉ! - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Addis Admas  >  Current Article

ወደ ቀያቸው የተመለሱ የቤኒሻንጉል ተፈናቃዮች እርዳታ ተቋርጦብናል አሉ!

By   /   July 16, 2019  /   Comments Off on ወደ ቀያቸው የተመለሱ የቤኒሻንጉል ተፈናቃዮች እርዳታ ተቋርጦብናል አሉ!

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 27 Second

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተፈናቅለው በኦሮሚያ ክልል ተጠልለው ለነበሩና ወደ ቀድሞ ቀያቸው የተመለሱ ከ70 ሺሕ በላይ የሚሆኑ ዜጎች የክልሉ አደጋ ሥጋት አመራር ጽሕፈት ቤት በመንገድ ብልሽት ምክንያት እርዳታ ማከፋፈል አለመቻሉ ታወቀ። ከቦሎጅንፎይና ያሶ ወረዳ ተፈናቅለው ሀሮ ሊሙ እንዲሁም ነቀምት ተጠልለው የነበሩት እነዚህ ተፈናቃዮች የሰብኣዊ እርዳታው በመቋረጡ ችግር ውስጥ መግባታቸውን አስታውቀዋል። በመስከረም 2011 ላይ በአካባቢዎቹ ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ከቀዬአቸው ተፈናቅለው የነበሩት ተመላሾቹ ከኢኮኖሚ እና ከሰብኣዊ እርዳታ መቋረጥ ችግሮች ባሻገርም የደኅንነትና የጸጥታ ሥጋት እንዳልባቸውም በተደጋጋሚ ሲገልጹ ይሰማል። ተፈናቃዮቹ ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሲመለሱ የመኖሪያ ቤታቸው በመውደሙ፣ የእርሻ መሬታቸው ከጥቅም ውጪ በመሆኑና መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን ማሟላት በማይችሉበት ሁኔታ ላይ በመገኘታቸው ድጋፉ መቋረጥ ከባድ አደጋ እንደጋረጠባቸው እንዳለው ተናግረዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ታረቀኝ ተሲሳ፣ ለተፈናቃዮቹ የሚቀርቡ ድጋፎችን የማዳረስና ማሰራጨት ችግሮች መኖራቸውን ተናግረው “በቂ የሆነ እርዳታ በክልሉ አለ፤ ነገር ግን በቡረ አና ሀሮ ሊሙ ወረዳ ለተጠለሉት ሰዎች እርዳታውን ለማድረስ በአካባቢው የመንገድ ብልሽት ሳቢያ ማድረስ አልተቻለም” ሲሉ ተናግረዋል። መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማስተባበር ሰብኣዊ ድጋፍ ለሁሉም ተፈናቃዩች እንዲዳረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ያስታወቁት ታረቀኝ፣ የክልሉ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት ችግሮቹን በአጭር ጊዜ ለመፍታት እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል። ከ73 ሺሕ በላይ የሚሆኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው የነበሩ ዜጎች ወደ ቀድሞ ቀያቸው የተመለሱ ሲሆን፣ እነሱን መልሶ ለማቋቋም የክልሉ መንግሥት 13 ሚሊዮን ብር መድቦ እየሠራ መሆኑም ታውቋል። ታረቀኝ እንደገለጹት፣ ተፈናቃዮቹ ከሥጋት ነጻ ሆነው ወደ ቀድሞ የማምረት ሥራችው በመመለስ እራሳቸውንና ቤተሰባቸውን መርዳት እንዲችሉ ከክልሉ መንግሥት ትልቅ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ለማለዳ ተናግረዋል። ሥራቸውን እንዲጀምሩም ለአርሶ አደሮች የእርሻ መሣርያ ማሰራጨትን ጨምሮ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል። በተመሳሳይ ባሳለፍነው ሳምንት በመተከል ዞን በተፈጠረው ግጭት፥ ከዳንጉር እና ፓዌ ወረዳዎች የተፈናቀሉ ከ3 ሺሕ በላይ ዜጎች 5 በሚሆኑ በመጠለያ ጣቢዎች ተጠልው እንደሚገኙም አመልክተዋል። ኹለተኛ ዙር እርዳታ ላልደረሳቸው ሰዎች እርዳታውን በአህያ፣ በፈረስና በጋሪ በመጠቀም ወደ ቦታው ለመላክ እንቅስቃሴ መጀመሩን ያወሱት ታረቀኝ፣ ለሕፃናቱ አልሚ ምግቡን በፈጥነት ለማድረስ እየተሠራ ነውም ብለዋል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

Traveler’s Alleged Crimes and Robbery at Bole Airport Raise Concerns

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar