www.maledatimes.com የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ቤተ መንግሥት የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበታል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ቤተ መንግሥት የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበታል

By   /   August 5, 2019  /   Comments Off on የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ቤተ መንግሥት የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበታል

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 29 Second

በንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ቤተ መንግሥት ውስጥ የተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሲገለገሉ መቆየታቸውን ተከትሎ ቅርሱ የተለያየ ጉዳት ስለደረሰበት የመፍትሄ እርምጃዎች መወሰድ ተጀመሩ። ከኹለት ዓመታት በፊት የምሥራቅ ጎጃም ዞን አስተዳዳሪዎች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ሲኖሩ የነበሩ ሲሆን ለዕድሳት በሚል እንዲወጡ የተደረገ ቢሆንም፣ በቅርሱ ውስጥ ሌሎች የመንግሥት ቢሮዎች እስካሁን እየተገለገሉበት ይገኛል።

ንጉሱ ባሠሩት የግብር አዳራሽ ውስጥ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩት የስብሰባ አዳራሽ፣ የጎጃም የባሕል ቡድን መለማማጃ፣ የምሥራቅ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ፖሊስ መምሪያ፣ ዐቃቤ ሕግና ሌሎች ቢሮዎች በመገልገል ላይ ናቸው። የምሥራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኀላፊ የኔነው ኹነኛው ለአዲስ ማለዳ እንዳስታወቁት ከሆነ፣ እነዚህ መገልገያ ቢሮዎች እንዲለቀቁ የታዘዘ ሲሆን፣ ከኹለት ዓመታት ጀምሮ ይደረጋል የተባለው ዕድሳት በተለያዩ ምክንቶች ሳይደረግ ቆይቷል።

“ከሩቅ አገር የንጉሥ ተክለ ሃይማኖትን ቤተ መንግሥት ለመጎብኘት የሚመጡ ሰዎች ቢሮ እንጂ የተከበረ ቤተ መንግሥት ሳያገኙ አዝነው ይመለሳሉ” ሲሉ የሄነው ተናግረዋል። የዞኑ ባሕል እና ቱሪዝም ቢሮም እንግዶች ሲሔዱ የነበረውን ታሪክ በቃል ከማስረዳት በዘለለ ቤተ መንግሥቱን ለማሳደስ የሔደበት ርቀት ደካማ እንደሆነ የዞኑ ባሕል እና ቱሪዝም የመዳረሻ ልማት ባለሙያ መስከረም ፈንታ ይናገራሉ። “የቤተ መንግሥቱ ቅጥር ግቢ ለክብሩ እና ለታሪኩ የሚመጥን ሥራ አልተሰራለትም” ሲሉም አክለዋል።

የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት የልጅ ልጆች በቤተ መንግሥቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ከመኖር በዘለለ ታሪኩን መጠበቅ እንዳልቻሉ የሚያወሱት መስከረም፣ ቤተ መንግሥቱን የዞኑ አስተዳደር እድሳት እንደሚደረግለት ቃል ገብቶ እንደነበርም ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል። ረጅም ዕድሜ ያስቆጠረውን ቤተ መንግሥት ታሪካዊ መልኩን እና ይዘቱን ሳይለቅ ለማሳደስ ሥራዎች እንደተጀመሩ ያስታወቁት የኔነህ በበኩላቸው፥ ቤተ መንግሥቱን ለማደስ በተደረገው የመጀመሪያ ዙር ጥናት 22 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ለክልሉ ምክር ቤት ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።

የኔነው ፍርድ ቤት፣ ፖሊስ ጣቢያ እና ዐቃቢ ሕግ በቀጣይ ዓመት ቤተ መንግሥቱን ለቅቀው አዲስ ወደ ተሠራላቸው ቢሮ እንደሚሔዱ ሲናገሩ ሌሎች ቢሮዎች ግን መቼ እንደሚለቁ የታወቀ ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።

ቤተ መንግሥቱን አድሶ የጎጃምን ባሕል እና ወግ የሚገልፁ ቅርሶችን እና በቤተ መንግሥቱ የነበሩ የቀደሙ ገዢዎች
ያስቀመጧቸውን ታሪካዊ ቅርሶች በአንድ ላይ አድርጎ ሙዚዬም ለማድረግ እንደታሰበ የኔነው ተናግረዋል። የደብረ
ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ጊዜያዊ እድሳት ለማድረግ ከባለሙያዎች ጋር ለመምከር ቀጠሮ መያዙንም አክለው ገልጸዋል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on August 5, 2019
  • By:
  • Last Modified: August 6, 2019 @ 3:23 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar