www.maledatimes.com ግልፅ ደብዳቤ ለአቶ ሽመልሽ አብዲሳ፤ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ግልፅ ደብዳቤ ለአቶ ሽመልሽ አብዲሳ፤

By   /   October 5, 2019  /   Comments Off on ግልፅ ደብዳቤ ለአቶ ሽመልሽ አብዲሳ፤

    Print       Email
0 0
Read Time:50 Second

Image may contain: 1 person, beard

” ስለሽመልስ አብዲሳ በሰጠሁት አስተያየት አሳስተህናል ለምትሉ ወገኖቼ ትልቅ ይቅርታ “

የተወሰንን ግለሰቦች ኦሮአማራ እያልን ስንጮህ ሕውሃት እና የኦነግ አጋሮች ሲሰድቡን ከረሙ፡፡ የእነርሱ መንጫጫት እንብዛም አሳስቦን አያውቅም ነበረ፡፡

አሁን ደግሞ በሚያስደነግጥ እና በሚያሳፍር ትችት እና ዲስኮርስ የአማራን እና የኦሮሞን ግንኙነት ለማክሰም ሞከርክ፡፡ ሆኖም ግን ለብዙ ዘመናት በአብሮነት የኖሩት ህዝቦች፤ በፓርቲና በግለሰቦች ፈቃድ ቀድሞውንም ያልተመሰረተ በመሆኑ ሊፈርስ አይችልም፡፡

እንደዚህ አይነት ሕውሃታዊ፤ኦነጋዊ እና አክራራዊ ገለፃ አንተ ይዘህ በመቅረብህ እኔ ብቻ ሳልሆን፤ ስትሾም “እንኳን ደስ ያለህ” ብለው መልዕክት የላኩልህ የፍልስፍና አሰተማሪዎችህም በእጅጉ አዝነውብሃል፡፡

አማራ ተባለ ነፍጠኛ በታሪኩ ለማንም ተንበርክኮ አያውቅም፤ ይህንን እውነታ እንኳንስ በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ያለ ሕዝብ ይቅርና፤ ቱርኮችም፣ ግብፃችም፣እንዲሁም ጣሊያኖችም ጠንቅቀው ያውቀሉ፡፡

ልጅ ሽመልስ እንደአስተማሪህ ያለኝ ምክር፡- በንግግርህ ላስቀየምከው ህዝብ ትልቅ ይቅርታ በይፋ ወጥተህ መጠየቅ ይኖርብሀል፡፡ በተጨማሪም ራስህን ሁን፣ ለሙገሳ እና የግለሰቦችን ቅቡልነት ለማግኘት ስትል ሌላውን ሰው ለመሆን አትሞክር፤ በተቻለህም መጠን የአክራራዊነት መንፈስ ከራስህ ላይ አርቅ፤ መጠቀሚያም አትሁን፡፡

በመጨረሻም፤
ስለሽመልስ አብዲሳ በሰጠሁት አስተያየት አሳስተህናል ለምትሉ ውገኖቼ ትልቅ ይቅርታ እጠይቃለሁ፤ለነገሩ የተከሉት ዛፍ ቀጥ ብሎ ይወጣል ሲሉ ከፍ ሲል ሊጎብጥ ይችላል እና እንዲሉ፡፡

ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on October 5, 2019
  • By:
  • Last Modified: October 5, 2019 @ 10:35 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar