www.maledatimes.com የእርሻ ምርታማነትን ማሳደግ የኢትዮጲያን ግብርና ዘርፍ ሙሉ ኢኮኖሚያዊ እሴት ለመጠቀም ወሳኝነት ተገለጸ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የእርሻ ምርታማነትን ማሳደግ የኢትዮጲያን ግብርና ዘርፍ ሙሉ ኢኮኖሚያዊ እሴት ለመጠቀም ወሳኝነት ተገለጸ

By   /   December 12, 2019  /   Comments Off on የእርሻ ምርታማነትን ማሳደግ የኢትዮጲያን ግብርና ዘርፍ ሙሉ ኢኮኖሚያዊ እሴት ለመጠቀም ወሳኝነት ተገለጸ

    Print       Email
0 1
Read Time:5 Minute, 33 Second

የዜና መዋእለ
እርሻ ምርታማነትን ማሳደግ የኢትዮጲያን ግብርና ዘርፍ ሙሉ  ኢኮኖያዊ እሴት ለመጠቀም ወሳኝ ነው
ዘመናዊ የግብርና ኩባንያዎች ምርጥ ዘሮችን ፣ፀረተባይ ኬሚካሎችን እና የተሻሻሉ የግብርና ዲጂታል ቴክኖሎጂ
ጆኒኔስበርግ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ታህሳስ 12, 2019/ — የአትዮጵያ ግብርና የሀገሪቱ የኢኮኖሚ መሰረት ሲሆን ከ 70% በላይ የሚሆነዉ የሃገሪቱ የሰው ሃይል የሚተዳደርበት ዘርፍ ነዉ፡፡ ግብርና ከሀገሪቱ ጠቅላላ የሀገር ዉስጥ ምርት አንድ ሶስተኛዉን የሚሸፍን ሲሆን ለሀገሪቱ የዉጭ ምንዛሬ  ማስገኛ ትልቁ ዘርፍ ነዉ፡፡ ይሁንና ኃላ ቀር የአስተራረስ ዘዴዎችና የምርታማነት ዝቅተኛ መሆን የሚያሳየው ግብርና በኢትዮጵያ ሊኖረው የሚችለውን  ሙሉ አቅም መጠቀም ዉስን አድርጐታል ፡፡ ከዚህ ዘርፍ ሊገኝ የሚችለዉን ምርት ማሳደግ እንደ ጤፍ ያሉ ዋና ዋና የሚባሉትን እህሎችን በአስተማማኝ ሁኔታ በማምረት በተለይም የዉጭ ገበያዉ ላይ ትኩረት በማድረግ ለኢኮኖሚዉ ዕድገት የሚኖረዉን አስተዋጽኦ ለማጎልበት ያግዛል፡፡ ኢትዮጵያ እንደ ቡና፣ የቅባት አህሎች፣ ጥራጥሬና አበባ በብዛት ለዉጭ ገበያ የምታቀርብ ሲሆን ዘመናዊ የአስተራረስ ዘዴዎችን መጠቀምና ምርታማነትን ማሳደግ በ ቀጣይ አጭር አመታት ውስጥ ከዘርፉ ልታገኝ የሚገባዉን  የዉጭ ምንዛሬ  በእጅጉ ሊያሳድገዉ ይችላል፡ የኢትዮጵያ መንግስት ከ 2007 – 2012 ዓ.ም ባዘጋጀዉ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ ግብርናዉን   በገቢ ምንጭነት ትልቁን ሚና እንዲጫወት ማስቀመጡ ለዘርፉ መልካም አጋጣሚን ይፈጥራል፡፡ ገበያ ተኮር የሆነ የተሳካ የእርሻ ስራ   የዘርፉን ምርታማነት በሰፊዉ ያሳድጋል፤ በገጠሩ የሀገሪቱ ክፍልም  በርካታ የስራ ዕድሎችን ይፈጥራል፡፡ ነገር ግን ብዙ ማነቆዎች ከፊት ተደቅነዋል፡፡ ከአነስተኛ ደረጃ እርሻ ወደ ገበያተኮር ግብርናበአሁኑ ወቅት ያለዉ የኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ በአብዛኛዉ አነስተኛ ይዞታ ባላቸው አርሶ አደሮች የሚከናወንና እርሻዉም በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ነዉ፡፡ ምርትና ምርታማነቱም ዝቅተኛ ነዉ፡፡ ይህም የሆነበት ዋናዉ ምክንያት አርሶ አደሮቹ እንደ ምርጥ ዘር እና  ፀረ ተባይ ያሉ የግብርና ግብዓቶችን  በቀላሉ ማግኘት ስለማይችሉ እና በአነስተኛ ማሳ ላይ የሚያመርቱትም  ገበሬዎች ዘመናዊዉን ቴክኖሎጂና የግብርና አያያዝ ዘዴን  ስለማይጠቀሙ ነዉ፡፡ ኢትዮጵያ ውስን የእርሻ  መሬት ፣ የአየር ሁኔታ መዛባት ፣ የመሬት መራቆት፣ ማሳዎችን ፋታ ሳይሰጡ በተከታታይ ማረስ፣ ባልተመቻቸ መጓጓዣ መጠቀምና አስፈላጊ የሆኑ የዘርፉ ክህሎቶች በበቂ ሁኔታ ባለመኖራቸዉ  ዘርፈ-ብዙ  ተግዳሮቶችን  ተጋፍጣለች፡፡  እነዚህን ተግዳሮቶች ለማሸነፍ የአገሪቱን የግብርና ዘርፍ ይበልጥ ሳይንሳዊ ፣ ይበልጥ የሚቌቌም እና የሚላመድ ይሆናል፡፡በሰፋፊ ማሳዎች ላይ ለሚከናወናዉ ገበያ ተኮር ለሆነው የእርሻ ስራ  የግብርና ፖሊሲ መኖሩ ከእያንዳንዱ ሄክታር የሚገኘዉን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ምቹ አጋጣሚን ይፈጥራል፡፡ በመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ የሚደረገዉ ኢንቨስትመንትና  የትራንስፖርት መሰረተ-ልማት መስፋፋት በረጅም ጊዜ የኢትዮጵያን ግብርና ለማሳዳግ ጉልህ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ደግሞ አርሶ አደሮች ምርጥ ዘርን እና ፀረ ተባይን እንዲጠቀሙ ማበረታታት፣ ዘመናዊ የግብርና ዘዴዎችን እንዲማሩ ማድረግ ምርታማነት በሰፊዉ እንዲጨምር ሊረዳ ይችላል፡፡በተጨማሪም  ዘመናዊ የግብርና ኩባንያዎች ምርጥ ዘሮችን ፣ፀረ-ተባይ ኬሚካሎችን እና የተሻሻሉ የግብርና ዲጂታል ቴክኖሎጂ አሰራሮችን በማቅረብ እነዚህን ጥረቶች ሊያግዙ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ ፀረ-አረምና ፀረ-ተባይን በቀጣይነት ማሻሻል ገበሬዎች ሰብሎቻቸዉን  ቀድመዉ  በመከላከልና በመንከባከብ ምርታማነታቸዉን እንዲያሳድጉ ያግዛቸዋል፡፡ በመላዉ ዓለም ያለዉ የምግብ ፍላጎት እየጨመረ ከመሄዱ ጋር ተያይዞ አርሶ አደሮች የተሻሉ ዝርያዎችን መጠቀማቸዉ ምርታማነታቸዉን በማሳደግ የወደፊቱን ሁኔታ አስተማማኝ ያደርጋል፡፡ ዘመናዊ በሳይንስ የተደገፈ የእርሻ ስራበመጪዎቹ አመታት ዉስጥ ገበያዉ ፍጥነቱን እየጨመረ ሲሄድ የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነታቸዉን ለማሳደግ ዲጂታል ቴክኖሎጂን መጠቀም የሚችሉ ይሆናል፡፡ የኢንተርኔት መረጃ መረቦችን፣ ሰዉ አልባ አዉሮፕላኖችን የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ሳይንሳዊ መሳርያዎችን በመጠቀም አርሶ አደሮቹ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አብዛኞቹን አንገብጋቢ ችግሮቻቸውን መፍትሔ እንዲያገኙላቸዉ ይረዳል፡፡ ዝመናዊ በሳይንስ የተደገፈ ግብርና ማለት ተፈጥሮአዊ ሚዛንን ሳያናጉ ወቅታዊ መረጃዎችን በመጠቀም ምርትን ፣ ዉሃ፣ ማዳባሪያ፣ ፀረ ተባይ ኬሚካሎችና አፈር በአግባቡ ተይዘዉ ከፍተኛ ምርት ማስገኘት በሚያስችል መልኩ መጠቀም ማለት ነዉ፡፡በዚህ ሂደት ዉስጥ የሳተላይት ምስሎች፣ ሰዉ አልባ አዉሮፕላኖች፣ ኢንተርኔት፣ መረጃ ሰጭና ተንታኝ  የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች በመለስተኛ ገበያ ተኮር እርሻ ላይ ለተሰማሩ አርሶአደሮች በቀላሉ የመጠቀም እድል ይኖራቸዋል፡፡ ምንም እንኳን ኢትዮጵያ  ባለፉት አስር ዓመታት የአገልግሎት ዘርፉ በፍጥነት እያደገና እየበዛ ኢኮኖሚዋን በተሳካ ሁኔታ  ማስፋፋት ብትችልም ግብርናዉን ማሳደግና ማዘመን ቀጣይነት ላለዉ የኢትዮጵያ  የኢኮኖሚ ዕድገት  ቁልፍ ሚና ይኖረዋል። አገሪቷ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ በግብርናዉ ዘርፍ በቀጣዮቹ ዓመታት  በዓለም ደረጃ ትልቅ ድርሻ እንዲኖራት የሚያስችላትን እድል ይፈጥራል፡፡

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 4 years ago on December 12, 2019
  • By:
  • Last Modified: December 12, 2019 @ 6:55 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar