www.maledatimes.com ፍርድ ቤቱ በጋዜጠኛ ጉዩ ዋርዮ ላይ ለፖሊስ ተጨማሪ የምርማራ ጊዜ ፈቀደ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ፍርድ ቤቱ በጋዜጠኛ ጉዩ ዋርዮ ላይ ለፖሊስ ተጨማሪ የምርማራ ጊዜ ፈቀደ

By   /   August 14, 2020  /   Comments Off on ፍርድ ቤቱ በጋዜጠኛ ጉዩ ዋርዮ ላይ ለፖሊስ ተጨማሪ የምርማራ ጊዜ ፈቀደ

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 30 Second

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2012 የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አረዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በጋዜጠኛ ጉዩ ዋርዮ ላይ ዛሬ ለፖሊስ ተጨማሪ የ10 ቀን የምርማራ ጊዜ ፈቅዷል። ተጠርጣሪው ጉዩ ዋርዮ አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን ቃለ መጠይቅ በማድረግ ፕሮግራሙን ቆርጦ በማቅረብ፣ ሰኔ 22 እና 23 ቀን 2012 ዓ.ም አመጽና ብጥብጥ እንዲነሳ በኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኦ.ኤም.ኤን) በመቀስቀስ ወንጀል ነው የተጠረጠረው።

ተጠርጣሪው ከሶስት ቀን በፊት በነበረው ቀጠሮ መርማሪ ፖሊስ ጋዜጠኛው አመጽ እንዲነሳ በተጠቀሰው ሚዲያ ቅስቀሳ ማድረጉን የሚያስረዳ የሰነድ ማስረጃ ማሰባሰቡን እና ተጨማሪ የምስክር ቃል መቀበሉን፣ በእጁ ላይ የተገኘ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ በፎረንሲክ እያስመረመረ መሆኑንም ማለዳ ሚዲያ መዘገባችን ይታወሳል በተጨማሪም በመረጃ ማሰባሰብ ዙሪያ ላይ ፣ ከኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሰልጣን እና ከተለያዩ ተቋማት ማስረጃ ለማሰባሰብና ቀሪ ምርመራ ለመስራት ተጨማሪ 14 ቀን እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን መጠየቁና ተጠርጣሪውም መቃወሚያ ማቅረቡን እንዲሁም የዋስትና ጥያቄ አቅርቦ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን መርምሮ ትእዛዝ ለመስጠት ለዛሬ ጠዋት ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።

በዚህም መሰረት በዛሬ ቀጠሮ የቀረበው ጋዜጠኛ ጉዩ ላይ መርማሪ ፖሊስ የጀመረው ምርመራ ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ ጊዜ እንደሚያስፈልገው ከግምት ውስጥ ያስገባው ፍርድ ቤቱ የ10 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜን ለፖሊስ ፈቅዷል። በሌላ በኩል የቀድሞ የኦፌኮ አመራር ደጀኔ ጠሃ እና የአቶ ጃዋር መሀመድ የኮምፒዩተር ሲስተም ባለሙያን አቶ ሚሻ አደም እና አቶ ኮርሳ ደቻሳ አመጽና ሁከት በመፍጠር ወንጀል ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀርበዋል። መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ በተጠረጠሩበት አመጽና ሁከት በማስነሳት ወንጀል ምርመራ እያከናወነ መሆኑን ጠቅሶ ለቀሪ ምርመራ የሰነድ ማስረጃ ለማሰባሰብ የምስክር ቃል ለመቀበል ተጨማሪ ጊዜ እንዲፈቀደለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው በቁጥጥር ስር ከዋልን ጀምሮ ፖሊስ ቃላችንን አልጠቀበልንም፣ ይህ አግባብነት የለውም፣ በፍትሃዊነት ፍርድ ቤቱ ሊያይልን ይገባል ሲሉ ያቀረቡትን አቤቱታ ያዳመጠው ችሎቱ የሁሉንም ጉዳይ በፍትሃዊነት እየተመለከተ መሆኑን አስርድቷል። ምርመራ እያከናወነ አይደለም ለሚለው መቃወሚያቸው ፍርድ ቤቱ በዛሬው እለት ጠዋት መርማሪ ፖሊስ ከመዝገቡ ጋር የሰራውን በተጠረጠሩበት ወንጀል የሰበሰበውን የሰነድ ማስረጃ ከመዝገቡ ጋር ማያያዙን በመጥቀስ ምርመራ በተገቢው እየተከናወነ መሆኑን ገልጿል። ተጨማሪ ምርመራ እንደሚያስፈልግ ከግምት ውስጥ በማስገባትም ለመርማሪ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ እንዲቀርብ የ10 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ፈቅዷል።

https://youtu.be/18nqI7AaN-g 

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 4 years ago on August 14, 2020
  • By:
  • Last Modified: August 14, 2020 @ 3:37 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar