www.maledatimes.com መንግስት ከህወሓት ወንጀለኞች ጋር ድርድር አይቀመጥም – አቶ ደመቀ መኮንን - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Addis Admas  >  Current Article

መንግስት ከህወሓት ወንጀለኞች ጋር ድርድር አይቀመጥም – አቶ ደመቀ መኮንን

By   /   November 19, 2020  /   Comments Off on መንግስት ከህወሓት ወንጀለኞች ጋር ድርድር አይቀመጥም – አቶ ደመቀ መኮንን

    Print       Email
0 0
Read Time:1 Minute, 13 Second
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት ከህወሓት ወንጀለኞች ጋር ለድርድር እንደማይቀመጥ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ተናገሩ።
አቶ ደመቀ መኮንን ከስዊድን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አን ሊንዴ ጋር በስልክ ተወያይተዋል።
ሚኒስትሩ በውይይታቸው በዋናነት መንግስት በትግራይ ክልል እየወሰደ ባለው የህግ ማስከበር ዘመቻ ላይ ትኩረት አድርገው መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
አቶ ደመቀ መንግስት በትግራይ ክልል እየወሰደ ካለው ህግን የማስከበር እርምጃ ጋር ተያይዞም ሊኖር ስለሚችል ድርድር፣ በትግራይ ክልል ስላለው የመገናኛና የሃይል አቅርቦት እንዲሁም መንግስት እየወሰደ ካለው ህግን የማስከበር እርምጃ ጋር በተያያዘ ለተፈናቀሉና ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ስለሚደረገው ሰብዓዊ ድጋፍ በተመለከተ ገለጸ አድርገዋል።
በማብራሪያቸውም የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስተዳደር ከህወሓት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማለሳለስ የሄደበትን ርቀት በተመለከተ ለሚኒስትሯ ገለጻ አድርገውላቸዋል።
መንግስት ለህወሓት በአዲሱ የመንግስት መዋቅር ውስጥ እንዲሳተፍ የሰጠውን በቂ ጊዜና እድል ቡድኑ ሳይጠቀምበት መቅረቱንም ገልጸዋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞም ቡድኑ ከስልጣን ከተወገደበት ጊዜ ጀምሮ ህገ ወጥ አካሄዶችን በመከተልና ፅንፈኛ ቡድኖችን በማደራጀት፣ በማሰማራትና በገንዘብ በማገዝ በሃገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ሲያሰማራ መቆየቱንም አስረድተዋል።
ከዚህ ባለፈም ቡድኑ በህገ ወጥ መንገድ በማን አለብኝነት ክልላዊ ምርጫ ማካሄዱንም ጠቅሰዋል።
ቡድኑ በሰሜን እዝ የሰራዊት አባላት ላይ የፈጸመው ጥቃት መንግስት በጁንታው የህወሓት ቡድን ላይ እርምጃ እንዲወስድ እንዳስገደደው ጠቅሰው፥ መንግስት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድርድር እንዲደረግ ያቀረበውን ሃሳብ እንደሚያደንቅም አንስተዋል።
ከዚህ ባለፈ ግን መንግስት ከህወሓት ወንጀለኞች ጋር ድርድር እንደማይቀመጥ ጠቅሰው፥ ጁንታውን ለህግ በማቅረብ ህገ መንግስቱን እንደሚያስከብርም አጽንኦት ሰጥተዋል።
አቶ ደመቀ አያይዘውም መንግስት አሁን ላይ ለተፈናቀሉና ተጋላጭ ለሆኑ ዜጎች ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር እየሰራ መሆኑን በመጥቀስም፥ በጁንታው ድርጊት የተስተጓጎሉ የመገናኛ እና የባንክ አገልግሎቶችን ዳግም ለማስጀመር እየሰራ ስለመሆኑም አውስተዋል።
Image may contain: 1 person, sitting
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

Traveler’s Alleged Crimes and Robbery at Bole Airport Raise Concerns

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar