www.maledatimes.com ኤርትራ ተረጋግታለች መገናኛ ሚንስትሩ ለጥያቄ ከመያዛቸው በቀር - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ኤርትራ ተረጋግታለች መገናኛ ሚንስትሩ ለጥያቄ ከመያዛቸው በቀር

By   /   January 22, 2013  /   Comments Off on ኤርትራ ተረጋግታለች መገናኛ ሚንስትሩ ለጥያቄ ከመያዛቸው በቀር

    Print       Email
0 0
Read Time:3 Minute, 30 Second

በሰኞ ማለዳ የተጀመረው የንጹሃን እና ፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ጥያቄ በዛሪእው እለት ረገብ ብሎ የዋለ መሆኑን አንዳንድ የዜና ምንጮች አትተዋል ። እንደ ምንጮቹ ዘገባ ከሆነ የፕረዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ልጅ በትላንትናው እለት ከማስታወቂያ ሚንስቴር ግቢ ውስጥ ታፍና የተወሰደች ሲሆን በ እለቱ የማስታወቂያ ሚንስትሩንም ለጥያቄ ይዘዋቸው እንዳሉ ለማወቅ ተችሎአል ከዚህ በላይ ምንም አይነት በሃገሪቱ ላይ ችግር አንፈጥርም ዋናው ነገር ጥያቄአችን በአግባቡ ይፈታ የሚል ታላቅ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ቀጣዩ የከፋ ሊሆን ይችላል ሲሉ ገልጠዋል። በሌላም በኩል ታፍኖ የነበረው የሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ጣቢያ ስርጭቱን የጀመረ ሲሆን ከተማዋ ወደ ቀድሞው ሰላማዊ አስተዳደሯን መቀጠሏ አንዳንድ የውጭ አምባሳደሮች ገልጸዋል አክለው ሲናገሩም አሁን በየመንገዶቹ ምንም የሚታይ የወታደራዊ መሳሪያም የታጠቀ ወይንም የተከበበ ቦታ የለም ሁሉም ቀድሞ እንደነበረ ነው ብለዋል ።አንዳንድ የተቃዋሚ ሚዲያዎች እንደሚሉት ከሆነ ለምሳሌ በአውሮጳ የሚንቀሳቀሰው አወቴ የተባለው የ ኤርትርያን የተቃዋሚዎች ራዲዮ ጣቢያ ሲናገር ይህ ጉዳይ ሲንቀሳቀስ የነበረው በተቃዋሚዎች የትግል ሃይል ሰራዊት ነበር ዋናው ጉዳይ ለውጥ ለማድረግ ነው ከ1983 ጀምሮ እስከአሁን ሃገሪቱ በአንድ የፖለቲካ ፓርቲ አስተዳደር ላይ ወድቃ ነው የምትገኘው ስለዚህ ይህንን ነገር መለወጥ ግዴታችን ነው ሲል ተናግሮአል ።Mapየፕረዚዳኑ ዳይሬክተር የሆኑት የማነ ገብረመስቀል በበኩላቸው ሰኞ እለት ከተማዋ ተረጋግታለች አሁን ወደ ቀድሞ ስራችን ተመልሰናል ብለዋል የተቃዋሚዎች “ሬዲዮ አወቴ”በበኩሉ የኢሳያስ አፈወርቂ ልጅ ተይዛ መወሰዷን ተናግሮአል

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 11 years ago on January 22, 2013
  • By:
  • Last Modified: January 22, 2013 @ 10:39 am
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar