www.maledatimes.com Responses to መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል> - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

Responses to መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል<<<<የፕሮፌሰር መጽሐፍ ብታንስም እውነት ናት>>>>>

By   /   March 14, 2013  /   Comments Off on Responses to መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል<<<<የፕሮፌሰር መጽሐፍ ብታንስም እውነት ናት>>>>>

    Print       Email
0 0
Read Time:20 Minute, 2 Second

የፕሮፌሰር መጽሐፍ ብታንስም እውነት ናት

ፕርፌሰር መስፍን ወ/ማርያም “መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ” የሚል ከደረቅ እውነቶች ፊት የቆመ# በይልኝታ ያልተሸረበ#በጥቅም ያልተኮማተረ# በፍርሃት ያልተሸበበ#……… መጽሐፍ ጽፈው አስነበቡን ፡፡ ዕውነት ለመናገር በትንሹ ከማንበብ በስተቀር መጣጥፍ ጽፌ ወይም አስተያየት ሰጥቼ አላውቅም ይህ የመጀመሪያዬ ነው፡፡እኒህ ያገር አጉማስ የሊቃውንት አድባር እንኳንስ የሚጽፉትን አንብቤ የሚናገሩትን አድምጬ ይቅርና ከነሙሉ ኢትዮጵያዊ ክብራቸው\ ከነሙሉ መንፈሳዊና አካላዊ ጥንካረያቸው በመጽሔቶች ላይ ፎቶግራፋቸውን ስመለከት የመልካም ኩሩ ዜጋ ብሐራዊ ስሜት እየተሰማኝ ክፉን ከዕርሳቸው አርቅ ስል እመኛለሁ፡፡
ይህ መጽሐፍ ድብቅ እውነቶችን ያወጋኝ#የአገሬን ታሪክ ከነጉድፉ የጀመረልኝ#ጥያቄዎቼን የጠየቀልኝ ስለመሰለኝ እነሆ ስሜቴን ልገልጽ ነው፡፡ እርሳቸው ……… ደልቶት የሞቀው የረጋ መንፈሱን እንዳይረብሽ መጽሐፌን አያንብበው እንዳሉት እኔም በቅን ልቦና የሚወደኝ ጥላቻን እንዳይገዛብኝ የእርሳቸውን መጽሐፍ ማንበብ የጠላ የእኔን አስተያየት ባያነበው ወዳጄ ነው፡፡ በጥንታዊት ኢትዮጵያ ህዝቦቿ እውቀት አፍላቂ የስልጣኔ ምንጭ ስመ ገናና እንደበሩ አሳይተውን በቅርቡ ዘመን ታሪካችን ግን ልጆቿ እውቀት ተቀባይ እውነትን ሳይሆን የተቀበልነውን ተራኪ ለውስጣችን ሳይሆን ለውጭ ያደርን አርጋጅ አጎንባሽ መሆናችንን ስም እየጠሩ ጊዜ እየቆጠሩ የምሁሮቻችንን ክሽፈት የነጋሲዎቻችንን ለሥልጣኔ’ ያልሆነች ኢትዮጵያ ባይነት የሃይማኖት አባቶቻችንን ሀብተ ሥጋ ወዳድነት የሚያቅለሸልሹ እውነቶች እያሉ በማስረጃ አረዱን፡፡ ግን ደግሞ ፈራ ተባ እያሉ ይሁን ሆነ ብለው ጠይቀህ መርምረህ ተረዳ ለማለት የሚያቅለሸልሹ ብቻ ሳይሆን የሚያስመልሱ እውነቶች እንዳሉ አይተው እንዳላዩ ስምተው እንዳልሰሙ ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡ለምሳሌ በአምስቱ ዓመት የተጋድሎ ዘመን ለጣሊያን ባንዳ የነበሩ ከነጻነት መልስ ግን የኃ/ሥላሴ ሹማምንት ለመሆን ከበቁትም ከተወነጀሉትም መካከል የቄሳር ጋዜጣ አዘጋጅ የነበሩት አፈወርቅ ገ/እየሱስ ብንጠቅስ የእኝህ ሰው ባንዳነት ትልቁን የጽናትና የመስዋዕትነት ተምሳሌት# ትልቁን የሞራል አርአያ አቡነ ጴጥሮስን “ህዝቡን አታስጨርስ ህዝብ ሊያሰለጥን አገር ሊያቀና የመጣ ገናና የስልጣኔ መንግሥት ነውና ለጣሊያን መንግሥት እደር ገዝቸሃለሁው” ያሉትን የሃይማኖት አባት ጉድፍ በምንም መልኩ አይወዳደርም፡፡ በዳኝነት ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ ለከንቱ ውዳሴና ለእንጀራ መቁረሻማ ስንቱ ባንዳ ነው የፍርድ (የችሎት) ውሳኔ እየተባለ የጀግና ወንድሞቹን አንገት በገመድ ያንጠለጠለ አናታቸውን በጥይት ያስተረተረ፡ ይሄ ተግባር እኮ በንጉሱም በደርግም የነበረ ዛሬም የዳበረ የብዙ ኢትየዮጵያውያን ወራዳ ሥራ ነው፡፡ በላይፍ መጽሔት ላይ የእገሌ አባት የመሐል ዳኛ ሆነው አቡነ ጴጥሮስ ላይ ፈርደዋል ይባላል ግን ማስረጃ አጥሯል ስላሉ ነው፡፡ አይደረግም ብለው ነው? ከየት ይለመዳል ከአያት ቅድመ አያት ነው እንጂ፣ እንዲህ ያለው ጽዩፍ ሥራ በዛሬው ዘመን ነውርነቱ ቀርቶ ተቀባይነት ያገኘና የሚያኮራ ሥራ የሆነ ይመስላል፡፡
በማስረጃ የተረጋገጠ#ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የተደራጀ የታሪክ እውነት ለትውልድ ባለመተላለፉ ሳይሆን አይቀርም በየዘመኑ ብቅ በሚሉ ምሁራን መካከል በዘር ላይ ያጠነጠነ የታሪክና የእውነትነት እሰጥ አገባ ትርምስ የሚከሰተው፣፣ ለምሳሌም ያህል ከቀደምቶቹ ነጋድራስ ገ/ህይወት ባይከዳኝና ነጋድራስ አፈወርቅ ገ/እየሱስ
ፕሮፌሰር መጽሐፉን በታተመበት ዘመን ወይም ወቅት እንዳልጻፉት ከውስጡ ባሉት መቼቶችና የግርጌ ማስታወሻዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡ምንአልባት ቀደም ብለው ቢጽፉትም የሚያስመልሱ የአሁኑን ዘመን እውነቶች እየጨመሩ ቢከልሱት ኖሮ መጠኑም እየጨመረ እንዳሉትም የተረጋገጡ እውነቶች ለትውልድ የሚተላለፉበት የታሪክ መማሪያ ዋጋነቱ የበለጠ ይሆን ነበረ የሚል ምኞት አለኝ፡፡ ለምን የአንተን ሳትወጣ ይህን ትመኛለህ እንደማይሉኝ ተስፋ አለኝ አቅመ ውሱንነቴና እጥረቴ አያወጣኝምና፡፡ የምኞቴ መሰረት የሚሆነው በእኛ ዘንድ በተገለጠ እውነት ተደፋፍኖ የተረጋገጠ እውነት እጥረት በመብዛቱ ታሪካችን ሁልግዜም በነበረው ላይ ከመጨመር ይልቅ የነበረውን አፍርሶ አዲስ መጀመርና ያለፈውን መውቀስ አዳብረናል፡ የአሁኑ ለራሱ ጥፋት እንኳን ያለፉትን መውቀስ ትልቁ ጥበቡ አድርጎታል፡፡ ታሪካችን በተጠኑ የታሪክ እውነቶች ላይ መመርኮዝ አለበት፡፡
ለምሳሌ፡- በአምስት ዓመቱ የአርበኝነት ዘመን በኋላ ባንዳ የነበሩ ሹማምንት ልጆችና ቤተሰቦች ምንያህል ለአገራቸው በጎ አስተዋጽኦ አበረከቱ? የባንዳነቱ ተጽዕኖ አድሮባቸውስ ምንያህል አሉታዊ ሆኑ? የሚለው ቢጠና መጭውን ትውልድ አያስተምርም? በነገራችን ላይ ይህን ሃሳብ በተመለከተ አንድ ነገር ላንሳ! ነፍሳቸውን ይማረውና ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ባንዳው አያታቸው ኢትዮጵያን# ኢትዮጵያዊነትንና ሰንደቅ ዓላማዋን የመጥላት ተጽዕኖ ሳያሳደሩባቸው ቀሩ ብላችሁ ነው? ለዚህም ይመስለኛል የቺሩሊን (የጣሊያንን) ውጥን በቋንቋ ላይ የተመሰረተ ሀገረ -መንግሥት ሽንሸና ከፍጻሜ ያደረሱት ያለበለዚያማ ከየት አመጡት ሌኒንም#ስታሊንም#ማኦም የሚጠሉት ሊብራሊዝምም ቋንቋ የህዝቦች ድንበር ይሁን አላሉም ከቺሩሊ በስተቀር፡፡ የጣሊያንን ምስራቅ አፍሪካ (Africa Orientale Italiana, or AOI) ካርታ ከአሁኑ የወያኔ የቋንቋ አሸናሸን (ክልል)ጋር አንባቢ ማነጻጸር ይችል ዘንድ በመጽሐፉ ከተካተቱት ካርታዎች ጋር ቢያካትቱት ኖሮ አስተማሪነቱ የጎላ ነበር፡፡በተገለጠ እውነት ተሸፋፍነው ሲያስፈልግ ለመቀስቀሸሻ ሲያስፈልግ ለመውቀሻ ሲያስፈልግ ለማደንዘዣ ከሚውሉት ያልተጣሩ ጉዳየዮች መካከል ፣-
• አጼ ዮሐንስ ወደመተማ ከመዝመታቸው በፊት በሸዋው ሚኒሊክ# በጎጃሙ ተ/ሃይማኖትና በእርሳቸው መካከል የነበረው የመልካም ወይም የቁርሾ ግንኙነትና ለመተማ ውድቀት የነበረው ድርሻ፡
• ሰሎሞናዊው ስርወ-ንግሥና ለአማራው ወይም ለሌላው አይገባውም የተቀባ አይደለም ስለሚለው አክሱማዊ ተምቤናዊ ትግሬያዊ የተገለጠ እውነት\ በትረ ሥልጣኑ በመዛነፉ ኢትዮጵያ ያልረጋች ሆነች ኢሰሜናዊ በሆኑ ህዝቦቿ እጅ የሥልጣኑ አልጋ በመውደቁ አገሪቱ ባሕር በር አልባና ለዛሬው ምስቅልቅል አስተዳደር ዳረጓት አሁን ወደ ጥንት ባለ እጆታዎቿ በመመለሷ ስልጣኔዋ አበበ ህዝቦቿ በለጸጉ ስለሚለው አደናጋሪ የውስጥ ለውስጥ የተገለጠ እውነት
• በሶማሊያና በሌሎች የዘመናት ጠላቶቿ ፓስፖርት በመጠቀም ከበረከት ኃ/ስላሴ ባለፈ ሌሎች ከስልጣን በላይ ምንም የለም በሚል አገራቸውን የከዱ ዳር ድንበሯን የሸጡ የሸቀጡ\ ለስልጣን ካበቃችሁን ኢትዮጵያን አረባዊ እናደርጋታለን ሲሉ ከነጋዳፊ ዙፋን ሥር የተንበረከኩ\ ለተራበው ህዝባቸው የተለገሳቸውን የጠኔ ማስታገሻ እህል እያዟዟሩ የሸጡ # ባገኙት ገንዘብ ለሥልጣን በሚደረግ ጦርነት የጦር መሣሪያ የገዙ\ በአደባባይ በይፋ ለባለጋራ ለተሰጠ የአገራችን ክፋይ መሬት ህዝባቸውን እልል በሉ አደባባይ ውጡ በማለት የቀለዱ…….. ለስልጣን ለሃብት ሲሉ የሸፈጡ በቂም በእልህ በጥላቻ የነሳስተው ገናናውን የሃገራቸውን ታሪክ የረገሙ ያኮሰሱ ኢትዮጵያውን እውነት ከማቅለሽለሽ አልፎ አያስመልስም? ነው ወይስ የዚህ ዘመን ሸፍጦች ሁሉ በታሪክ ይመርመሩ በሚል የተተወ፡፡በእኔ እምነት የመጽሐፉ ዓላማ የተረጋገጠ እውነት ለትውልድ ለማጋራትና ሌላው እንዲጨመርበት በመሆኑ እንዲህ ዓይነት እውነቶች ተመርምረው ተጨምረውበት ቢሆን በታሪክ ውድነቱን አይጨረውም ነበር?
• በኃ/ስላሴ#በዘውዲቱ #በእያሱ መከካከል ተዳፍነው የቀሩ እውነቶች……..
• ለመጽሐፋቸው ንዑስ ርዕስ ያደረጉት፡-
ኢትዮጵያ ሃገሬ ሞኝነሽ ተላላ
የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ
የሚለው ግጥም በእርግጥ የዮፍታሔ ንጉሴ አይደለም?
ከላይ በግርድፍ ያነሰኋቸው ሃሳቦች ፕሮፌሰር በመጽሐፋቸው ገጽ 199 ላይ አንስተው በእንጥልጥል ከተዋቸው የብዙውን ሰው አእምሮ ከሚቆጠቁጡ ያልጣሩ እውነቶችና ሌሎች ያልተነካኩ የተገለጡ እውነቶችን አካትተውና ጨማምረው በሌላ መጽሃፍ እናነባቸው ይሆን ከሚል ቀና ምኞት የመነጨ እንጂ ለመንቀፍና ለመተቸት ቅንጣት ታክል እንኳን እንዳልሆነ አንባቢ ሁሉ ይረዳልኝ፡፡
ፕሮፌሰር በብዙ ጽሑፎቻቸው ላይ እንደሚገልጹት በዚህ መጽሐፍም ታሪካችን “ማሰብ ክልክል ነው” በሚል ዓይነት በታሰረ የሰዎች ህሊና ከማሰብ ከማሰላሰል ርቆ የተሰጠውን ብቻ የሚቀበል አእምሮ ስንገነባ መኖራችንን ልብ ላለው ልብ ይላል፡፡ በአሁነኑ ዘመን ከዚህ አላለፈም ብለው ነው? ጥንትስ ባደበባባይ “ማሰብ ክልክል ነው” ቢባልም ሰው በቤቱ በጓዳው በነጻ ህሊናው ከፈጣሪ በታች ነገሥታቱን ያማ ነበር፡፡አሁን አሁንማ የተሰጠን አዋጅ መቼ “ማሰብ ክልክል ነው” በሚል አበቃ ህሊናችን # ማሰቢያችን ታሽጓል የሚል ማኅተም ታተመበት እንጂ\ የአእምሮሯችን ጓዳ በቁልፍ ተከረቸመ እንጂ\ ማሰላሰያችን ተለጎመብን እንጂ እንዲያው በጥቅሉ አዋጁ ጠበቀብን እንጂ መች ላላልን፡፡ማኅማችን ጥርነፋ ነው\ ቁልፋችን አንድ ለአምስት ነው \ ልጓማችን ግምገማ ነው፡፡
ታሽገን እንዳንቀር ተቆልፎብን እንዳንዝግ ተለጉመን እንዳንዝል እናንተን ማስተንፈሻ እናንተን ማስታገሻ አገኘን ሳይደግሥ አይጣላም ይባል ይሆን! እናንተ ለእኛ ጭንቅ ሲበዛ መፈናፈኛዎቻችን እውነት ሲጠፋ መባዘኛዎቻችን በድቅድቅ ጨለማ ማጮለቂያዎቻችን ናችሁ፡፡ አሁን አሁን የቃሊቲው ወሳጅ መፈናፈኛችንን እያጠበበ መባዘኛችንን እየለቀመ ማጮለቂያችንን እየደፈነ በዝምታ እንደወጠረን አካለችንን እንዳገረረው ህሊናችንን እንደሰበረው በእኩይ ምግባሩ እንደተጋ ነው፡፡ እኛስ መፈናፈኛው ሲጠፋ መሰናዘሪያው ሲያከትም እንደበርሜሉ እንፈነዳ እንደ ፊኛው እንተረተር ይሆን? ማን ያውቃል? ለማንኛውም አሁን እናንተ ለእኛ እስካሪኮ ናችሁ ማስተንፈሻ፡፡

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 11 years ago on March 14, 2013
  • By:
  • Last Modified: March 14, 2013 @ 7:02 am
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar