www.maledatimes.com “ምጥ” ========= (የኢትዮጵያ – ምጥ) - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

“ምጥ” ========= (የኢትዮጵያ – ምጥ)

By   /   December 1, 2013  /   Comments Off on “ምጥ” ========= (የኢትዮጵያ – ምጥ)

    Print       Email
0 0
Read Time:6 Minute, 31 Second

በወሰን ሰገድ ገብረ ኪዳን
በአፍላ የወጣትነት ዘመኑ ወደዳት፡፡ መውደድ ቢሉ መውደድ ነው፡- ቅልጥ ያለ ፍቅር ያዘው፡፡ በፍቅሯ ቀለጠ፤ ተቅለጠለጠ፡፡ እሷም እንደሱ በፍቅሩ ተነደፈች፡፡

በየፊናቸው መፋቀርን ፈቀዱ፡፡ ተፈቃቀዱ፡፡ የእሷ እናት የአጋጣሚ ነገር ሆኖ እናት ዓለም ነው ስማቸው፡፡ “እናት” ይሏቸዋል ሲያቆላምጣቸው፡፡ “የዓለም ይሁንላችሁ” ብለው ፈቀዱላቸው፡፡ ዳሯቸው፡፡

ተጋቡ፡፡ በተክሊል፡፡ በቃልኪዳን፡፡

በዓመቱ አናት መልዕክተኛ መጣባቸው፡፡
በወሰን ሰገድ
“ሴት ልጅዎ …. ኢትዮጵያ ምጥ ይዟታል፤ ይድረሱላት” ተባሉ፡፡

ነጠላቸውን እንኳ በወጉ ሳያጣፉ እየበረሩ ወደልጃቸው ሄዱ፡፡

ሲደርሱ እሱ ኢትዮጵያን በመኪና ወደ ሆስፒታል ሊወስዳት አቆብቁቧል፡፡ አብረውት ሄዱ፡፡ ወዲያው ሐኪሞቹ ተቀብለው ወደማዋለጃ ክፍል አስገቧት፡፡

“እናት” ማዋለጃው ክፍል ብር አጠገብ ተቀምጠው እየተንቆራጠጡ መጠበቅ ጀመሩ፡፡ እሱ ረዥሙ የሆስፒታሉ ኮሪደር ላይ እየተመላለሰ መንቆራጠጡን ቀጠለ፡፡

ጠበቁ፡፡ ጠበቁ፡፡ የምስራች ጠበቁ፡፡ ምንም ነገር የለም፡፡ “እናት” የኢትዮጵያን የተፋፋመ የምጥ ጩኸት ብቻ ነው የሚሰሙ፡፡ እሱም የምጧ ጩኸት በሩቁ ይሰማዋል፡፡ ተጨንቋል፡፡ ጭንቀቱ ከወዲያ ወዲህ ያንቆራጥጠዋል፡፡

“እናት” ግራ ተጋቡ፡፡ ኢትዮጵያ ማዋለጃ ክፍል ቀገባች ሰዓታት አልፏል፡፡ በሃሳብ እና በጭንቀት እየናወዙ ወደ እሱ ሲመለከቱ ድንገት ቀበቶ መታጠቁን አዩ፡፡

“ና ና! ና እስቲ ወዲህ አንተ!…ና እኮ ምልህ?…እንዲህ ነችና!….ቀበቶ አልገህልኛል!?” አሉት ቆጣ ብለው፡፡

“አዎና!….. ካለቀበቶ ሱሪ ልታጠቅ ነው እንዴ!?…ምነው!?”

“በል ቀበቶህን ፍታ!!….ፍታና አውልቀው!….አንተ ቀበቶ አስረህ ነው ለካ የኢትዮጵያ ማህፀን አልፈታ ያለው!!” ሲሉ አዘዙት ካስተር ኮምጨጭ ብለው፡፡

እየገረመው ቀበቶውን ፈታና አጠገባቸው አስቀመጠው፡፡ እናም መንጎራደዱን ቀጠለ፡፡ “እናት” በተቀመጡበት ወገባቸውን ጭምቅ አድርገው ይዘው ይንቆራጠጡ ገቡ፡፡

አሁንም የኢትዮጵያ የምጥ ጣር ጩኸት ከማዋለጃ ክፍሉ ውስጥ እየሾለከ ከመሰማቱ በቀር መልካም የምስራች መስማት አልተቻለም፡፡

እንዲሁ በየፊናቸው ሲንቆራጠጡ ደቂቃዎች እንደዘበት ነጎዱ፡፡ እሱ ተበሳጨ፡፡ ጭንቀቱ የፈጠረው ብስጭት አንዳች ሃሳብ ወደ ህሊናው አመጣለት፡፡ ያን ሃሳብ እያሰላሰለ ወደ “እናት” ጠጋ ብሎ ጠየቃቸው፡፡

“እናት፤ ኢትዮጵያ ምጧ የበረታው እኔ ቀበቶ በማሰሬ የተነሳ ነው በለውኝ ቀበቶ ፈታሁ፡፡ ከፈታሁ በኋላም አልወለደችም፡፡ ለምን ይመስልዎታል!?”

“ቀድሞውኑ ብትፈታ ኖሮ ይኼኔ ኢትዮጵያ ወልዳ ነበር፤ ቀበቶ ማሰርህ ነው ማህፀኗን ያሰረው” አሉትና ፊታቸውን ወደማዋለጃው አዞሩ፡፡

“እንደዛ ከሆነ ጫማዬንም አስሬአለሁ ልፍታው”

“ፍ….ታ ….ው!!” አሉት በለበጣው ተናደው፡፡

ንዴታቸውን ላለማባባስ ፈታው፡፡

የጫማውን ክር ፈትቶ ቀና ሳይል የእልልታ ድምፅ ሲያስተጋባ ሰማ፡፡

ኢትዮጵያ ወለደች፡፡

ይኼኔ እሱ እንዲህ አለ ለራሱ፡-
“ኢትዮጵያ ቀበቶ የሚያወልቅና ጫማ የሚፈታ ትውልድ ወለደች” አለ፡፡

ሣቀ፡፡ በራሱ ሣቀ፡፡ በልጁ ሣቀ፡፡ በሣቁ ከ“ምጡ” ተገላገለ፡፡

(ሕዳር 22 ቀን 2006 ዓም ከለሊቱ 8 ሰዓት ተፃፈ)

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 10 years ago on December 1, 2013
  • By:
  • Last Modified: December 1, 2013 @ 7:52 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar