www.maledatimes.com ድርድር… የወያኔ የማዘናጊያ እና የማጭበርበሪያ ደውል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ድርድር… የወያኔ የማዘናጊያ እና የማጭበርበሪያ ደውል

By   /   December 2, 2013  /   Comments Off on ድርድር… የወያኔ የማዘናጊያ እና የማጭበርበሪያ ደውል

    Print       Email
0 0
Read Time:7 Minute, 15 Second

ምንሊክ ሳልሳዊ :- ወገኖቼ መቸም የወያኔን እኩይ ምግባር የቱን ጥለን የቱን አንስተን እንደምንናገር አናውቅም ሙሉ ሰውነቱ በመጥፎ የፖለቲካ ፈንጂዎች እና በቀሎች የተሞላ በማዘናጋት እና በማደናበር በማጭበርበር የተሞላ መሆኑ ሳይታለም በይፋ የተፈታ እውነት ነው::

የዛሬ ትኩስ ወሬ የሆነው የወያኔው ጁንታ ከግንቦት ሰባት ጋር እንደራደር የሚለው ጥያቄ እጅም አስገራሚ የማይደንቅ ሆኖም በጭንቅ ሰአት የተጠበቀ የፖለቲካ ገመድ ጉተታ አሊያም ማጭበርበር ሲጨመርም ማዘናጋት የታከለበት ጠማማ አክሄድ መሆኑ ለማንም አይጠፋውም:: ወያኔ ከበረሃ ጀምሮ በአባቱ ሻእቢያ በኢሕኣፓ በደርግ በኢሕዴን እና ተመሳሳይ አንጃዎች ላይ ሲሰራ የነበረው የማጭበርበር እና የማዘናጋት ፖለቲካ አልፎ እስከ ሽብር ተግባር ድረስ የሚፈጽም አደገኛ አሸባሪ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል::ወያኔ በአሲምባ ኢሕኣፓን በሮም እና ሎንዶን ደርግን እንዲሁም በበረሃ ሻእቢያን እና ኢህዴንን… ከዛም የሽግግር መንግስት ከተባለ ጀምሮ እንደ ኦነግ ኦብነግ የመሳሰሉ ድርጅቶችን በድርድር ስም ሲያጭበረብር የነበረ ከመሆኑም በላይ በትልቁም የኢትዮጵያን ሕዝብ ያጭበረበረ እና እያጭበረበረ እያዘናጋ ያለ ቅስም ለመስበር የሚራውጥ የሽብር ጀሌ ነው::

ወያኔ አሸባሪ ብሎ ከፈረጀው ግንቦት ሰባት ጋር ለመደራደር ያቀረበው ጥያቄ አንድም ቀልድ ነው አንድም ማዘናጊያ ስልት ነው:: ወያኔ በሃገር ውስጥ ያለውን ሕዝብ እና ከሃገር ውጪ ያለውን ዲያስፖራ ለማዘናጋት እና ከገባበት አጣብቂኝ ለመውጣት የመጀመሪያውን ዳገት በመቧጠጥ ላይ ይገኛል::የወያኔው ጁንታ ያቀረበው የድርድር ጥያቄ ወጥሮ የያዘውን ከፍተኛ አደጋ ለመወጣት ሲሆን ከዚህም መሃል

-በሃገሪቱ ይከሰታል ተብሎ የሚሰጋው እና በጥናት ሪፖርት የቀረበበት የኑሮ ውድነት
-በሰራዊቱ እና በደህንነቱ ተቋማት ውስጥ እየተነሱ ያሉ ህገመንግስታዊ ጥያቄዎች
-በተለያዩ ሃገሮች በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሱ ያሉ ብሄራዊ ውርደቶች
-የሃይማኖት መሪዎች ወቀሳ እና የሃይማኖት ነጻነት ጥያቄ
-በሃገሪቱ እየተስፋፋ የመጣው የትውልዱ ስራ ማጣት እና ስደት
-የፖለቲካ ምህዳኡ መጥበብ ያስነሳው አለማቀፍ ጫና
-በየእስር ቤቱ ያሉ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች ይፈቱልን ጫና
-እንዲሁም ተመሳሳይ የሆኑ የዲሞክራሲያዊ መብቶች እና የፖለቲካ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ለውጦች ጥያቄዎች ወያኔን አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ሲሆን በየጊዜው በሚነዙ ፕሮፓጋንዳዎች እና በማይገናኚ የሃሰት እይታዎች የሚዲያ ፍጆታ የፖለቲካ ውሸቶች ሕዝብ በጁንታው ላይ ያለውን እምነት በማጣቱ እና ተስፋው በመሟጠጡ ወያኔ በውጥረት ውስጥ በመሆኑ ይህንን ለማዘናጋት እና የፖለቲካ ማጭበርበር ለመፈጸም የድርድር ጥያቄዎች ማቅረቡ ምንም አዲስ ነገር ካለመሆኑም በላይ የሚጠበቅ እና የማዘናጊያ ደውል ነው:; ከዚህ ቀደም ተደራደርኩ ካላቸው ድርጅቶች ላይ ያመጣው ታጣ እና ውጤት ቢኖር ስደት እና ሞት ለድርጅቶቹ አባላት እንዲሁም አሸባሪ የሚል ታርጋ መለጠፍ ብቻ ነው::

በግንቦት ሰባት ውስጥ ያሉ ታጋዮች በኢህኣፓ በኢሕኣዴግ በቅንጅት እና በተለያዩ ፓርቲዎች ውስጥ በመሆን የተለያዩ እውቀቶችን እና ልምዶችን የቀሰሙ እንደመሆናቸው ለወያኔ የማዘናጊያ እና የማጭበርበሪያ ደውል መልስ አይጠፋቸውም ትግሉም ስልጠናውንም ሃገር እና ወገን የማዳን ስራውም ከበፊቱ በበለጠ መልኩ እየተጠናከረ እንደሚሄድ እንተማመናለን::
‪#‎MINILIKSALSAWI‬
ለወያኔ የማደናበሪያ እና የማዘናጊያ ስልቶች የሚራራ ልብ የለንም!! ድል ለተጨቆኑ ሕዝቦች!!እናቸንፋለን!!!

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 10 years ago on December 2, 2013
  • By:
  • Last Modified: December 2, 2013 @ 10:35 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar