በኢትዮጵያ የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሐምሌ 28 ቀን 2009 ዓ/ም ይጠናቀቃል | መንግስት በይፋ አዋጁ እንደሚነሳ አላሳወቀም
(የጀርመን ድምጽ ራድዮ) መስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም. በኢትዮጵያ የታወጀዉ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ሐምሌ 28 ቀን 2009 ዓ/ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። በመንግሥት በኩል ሰላምና መረጋጋት ወደ ቦታዉ መመለሱን ቢገልፅም እስካሁን በይፋ አዋጁ እንደሚነሳ አላሳወቀም። ከማሕበረሰቡ በኩልም ቢሆን ሰላምና መረጋጋት ሰፍኗል መነሳት አለበት ቢሉም፣ ገሚሱ ደግሞ አሁንም በተለያዩ ቦታዎች ችግሮች ስላሉ አዋጁ መነሳቱ ላይ ጥርጣሬ […]
Read More →የህወሃት ደኅንነቶች የኮሎኔል ደመቀን የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ለመጥለፍ ሙከራ አደረጉ | በኮሎኔሉ ላይ 9 የሰለጠኑ ምስክሮች ቃላቸውን ሰጥተዋል
ከሙሉቀን ተስፋው በጀግናው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ቤተሰቦች ላይ የደኅንነቶች ጫና ተባብሶ መቀጠሉ ተሰማ፡፡ የኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የክስ ሒደት እየታየ የተዘጋጁ ምስክሮች ፍርድ ቤት ቃላቸውን በሚሰጡበት ሰዐት ሐምሌ 3 ቀን 2009 ዓ.ም. የአገዛዙ ደኅንነቶች የኮሎኔሉን የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ጠልፈው ለመውሰድ ሲሞክሩ በሕዝብ ርብርብ መክሸፉን በአካባቢው የነበሩ እማኞች ገልጸውልናል፡፡ እድሜያቸው በ20ዎቹ ውስጥ የሚገመቱ ወጣት […]
Read More →ወርሃዊ የሰብዓዊ መብቶች ሁነቶች አጭር ማጠቃለያ | ሰኔ 2009 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ፕሮጀክት (ኢሰመፕ) የተዘጋጀ 1. የመሬት መብት ተሟጋቹ ኦሞት አግዋ ቀሪ መከላከያ ምስክራቸውን ያሰሙት ባሳለፍነው ሰኔ ወር ነበር፡፡ የመሬትና አካባቢ ጥበቃ አክቲቪስት ኦሞት አግዋ ሰኔ 05/2009 ዓ.ም ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ቀሪ ሁለት የመከላከያ ምስክሮችን አስደምጠዋል፡፡ ምስክሮቹ በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው የጋመቤላ ክልል ፕሬዝዳንት ኦኬሎ አኳይ እና አቶ […]
Read More →“ማእከላዊ ውስጥ ሴትነቴን ተመስርተው ጥቃት ፈጽመውብኛል” – አክቲቪስት ንግስት ይርጋ
#Ethiopia #AmharaProtests #FreeNigist ስም፡- ንግስት ይርጋ ተፈራ ዕድሜ፡- 24 አመት አድራሻ፡- ጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 አሁን በእስር የምገኝበት፡- ቃሊቲ እስር ቤት ለእስር የተዳረግሁበት ምክንያት፡- በሀምሌ ወር 2008 ዓ.ም በጎንደር ተደርጎ የነበረው ህዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ላይ ተሳትፎ አድርገሻል የሚል ነው፡፡ በይፋ የተመሰረተብኝ የክስ አይነት፡- የሽብር ክስ ሲሆን (‹‹ህዝባዊ አመጾችን››) በማደራጀትና በሰልፎቹም በመሳተፍ ‹‹የሽብር ቡድኖችን ተልዕኮ […]
Read More →የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ የመዝጊያ ዝግጅት ላይ ለምን ብጥብጥ ተነሳ? | ሪፖርታዥ
Zehabesha Media With Maleda Times (ዘ-ሐበሻ) ለ34ኛ ጊዜ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ስፖርት እና ባህል ፌስቲቫል በዋሽንግተን ግዛት ትልቁ ከተማ ሲያትል ለአንድ ሳምንት ያህል እጅግ በደመቀ ሁኔታ ተካሂዶ በሚያሳፍር መልኩ ተጠናቋል:: በሲያትል በተደረገው የስፖርት ፌስቲቫል ላይ በርካታ መልካም ነገሮችን እንዳየነው ሁሉ ጥቂት የሚያሳፍሩና ወደፊት ሊታረሙ የሚገባቸው ድርጊቶችን ተመልክተናል:: ይህን የሰሜን አሜሪካ የስፖርት ፌዴሬሽን ኢትዮጵያውያን ታግለው ከአላሙዲ […]
Read More →የሰሜን አሜሪካ እግርኳስ ጨዋታ መዝጊያ ዝግጅት በብጥብጥ ተፈጸመ !!”በጣም ታሳፍራላችሁ ይሄ የኢትዮጵያዊነት ባህል አይደለም ” ፌደሬሽኑ
34ኛው የሰሜን አሜሪካ እግርኳስ ጨዋታ ፕሮግራም ባለፈው ሳምንት ተጀምሮ በትላንትናው እለት 7/8/2017 የተፈጸመ ሲሆን በመዝጊያ ፕሮግራም ላይ የተዘጋጀው የሙዚቃ ዝግጅት ላይ በሰአቱ ዝግጅቱ ባለመከናወኑ እና ሙዚቀኞች በሰአቱ ባለመግባታቸው ታዳሚውን ህዝብ አስቆጥቶአል ። ከለሊቱ ሁለት ሰአት ላይ በሙዚቃ አዳራሹ የገቡት ጃኪ ጎሲ እና አብነት አጎናፍር ሲሆኑ ሌሎች የሙዚቃ ባንዶች እና ብዟየሁ ደምሴ እና ራስ ባንዶችን በወቅቱ […]
Read More →የቴዎድሮስ ካሳሁን ሙዚቃ አገር አፍራሽ ነው ( ጋዜጠኛ እና ጠበቃ ልጅ ተክሌ)
በሰሜን አሜሪካ በተከናወነው የእግርኳስ ጨዋታ ላይ ከተለያዩ አለማት የተገናኙት የኢትዮጵያ ነጻ ጋዜጠኞች ማህበር ከፍተኛ ውይይት በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ አድርገዋል ከዚህም መካከል የቀድሞው የእሳት ጋዜጠና ልጅ ተክሌ ጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ በቴዎድሮስ አፍሮ የ2017 ሙዚቃ ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ይህንን ልዩ ፕሮግራም ሙሉውን አቅርበንላችኋል ። ማለዳ ታይምስ ህብር ሬዲዮ እና ዘሃበሻ በጋራ በመተባበር ማቅረባችንን […]
Read More →ሐመልማል አባተ ይቅርታ ጠየቀች – “አንድ በሚያደርገን ነገር ላይ እናተኩር” “ሰዎች ነን እና ሁላችንም እናጠፋለን” !
ከአስራ አራት አመት በሁዋላ የሙዚቃ ዝግጅቷን ለማቅረብ ጎራ ያለችው ሃመልማል አባተ ፣ ከነበራት ናፍቆት ጋር ተነስታ ባለፉት ጊዜያቶች ከወያኔ ህወሃት ጋር የነበራትን የስራ ቁርኝት አስመልክታ የይቅርታ ሃሳብ ያቀረበች ሲሆን ማንኛውም አርቲስ እንዳልወከላት እና በእራሷ ተነስታ የይቅርታ ምህረት ጥያቄ ማቅረቧን በመድረኩ ላይ ከተናገረችው ሃሳብ ሊደመጥ ተችሏል ። አርቲስቶⶫችን ስህተት ሲሰሩ ብንመካከር እና ከጥፋታቸው ብንመል ይሻላል እርር […]
Read More →
