www.maledatimes.com ዲይስፖራ ፖለቲከኞች እና ወያኔ = ለሃገር የማይበጁ የጥላቻ አንጃዎች‪ የህዝብን አንደበት እንተነፍሳለን:: ‪ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ዲይስፖራ ፖለቲከኞች እና ወያኔ = ለሃገር የማይበጁ የጥላቻ አንጃዎች‪ የህዝብን አንደበት እንተነፍሳለን:: ‪

By   /   December 24, 2013  /   Comments Off on ዲይስፖራ ፖለቲከኞች እና ወያኔ = ለሃገር የማይበጁ የጥላቻ አንጃዎች‪ የህዝብን አንደበት እንተነፍሳለን:: ‪

    Print       Email
0 0
Read Time:7 Minute, 4 Second

MINILIKSALSAWI‬

ምንሊክ ሳልሳዊ ሁለቱን በየፈርጃቸው በትግል አካሄዱ ዙሪያ ስንመለከታቸው የፖለቲካ አጀንዳቸውን በኢኮኖሚ በደቀቀው ህዝብ እና በነጻነት ጥያቄ በሚያነባው ህዝብ ላይ ለመጫን እየተራወጡ የሚሄዱ በጥላቸ የተሞሉ አንጃዎች ናቸው:: የወደደ ይውደድ የጠላ ይጥላ የህዝብን አንደበት ግን እንተነፍሳለን::ምናልባት ወያኔን ተወት አድርጓት እና ዲያስፖራ ፖለቲከኛ ነኝ ጋዜጠኛ ነኝ የሚለው ጣማማ እና በጥላቻ የሚያነክስ ይህ ነገር ላይዋጥለት ይችላል::
===== መዋጥ ከቻለ ይዋጥ መወጥ ካልቻለ ያስመልሰው የራሱ ጉዳይ::=======

እኛ አንዴ በሃገር ውስጥ አንዴ በውጭው በስራ ጉዳዮች የምንኖር ዜጎች ከወያኔ በባሰ መልኩ እያንገበገብን ያለው በአውሮፓ እና በአሜሪካ ተደብቆ መሰሪ እና በሃገር ላይ የጥላቻ ድብቅ አጀንዳውን እያራመደ ያለው ፖለቲከኛ ነውሃገር ወዳድ በሰው አገር የሚከራተቱ ዜጎችን ከግራ ቀኝ በተደቋቆሰ ፖለቲካ የሚያላትመው እና የዲያስፖራውን ሃገራዊነት ካለሞሶሶ ለማስቀረት የኢቶጵያን ህዝብ ትግል የሰው ሃገር የመኖሪያ ፍቃድ ማስገኛ ያደረገው የዲያስፖራ ፖለቲከኛ የጥላቻ ፖለቲካ ተሞልቶ ዘላለሙን በወሬ ትግሉን እየገደለው ይገኛል:: በሃገር ቤት ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በከፍተኛ ፍጋት ውስጥ ሲያሳልፉ ግማሹ ትግሉን መጦሪያ ሲያደርገው የኢትዮጵያን ህዝብ ከጭቆና አገዛዝ ማላቀቅ አልተቻለም::

የወያኔ ካድሬዎች ከሕወሓት መራሹ መንግስት የሚያገኙትን ጥቅም ለማስጠበቅ በከፍተኛ ጥላቻ ተሞልተው በሃገር ውስጥ በህዝብ ስቃይ ሲደሰቱ የተቃወመውን ሁሉ በማፈን በመግደር ወደ ኢስር ቤት በመወርወር የተቃወመ ሁሉ ጠላት ነው በሚል የእኛ እናውቅላቹሃለን አስተሳሰብ ተሞልቶ ህዝብን ሰቆቃ ውስጥ ከቶታል በፍራቻ አንገቱን ሰብሯል:: ውስጥ ለውስጥ በሚነዛ ሽብር የህዝብ ሚዲያዎችን ለፓርቲ ፍጆታ በማዋል በሚደረጉ የፕሮፓጋንዳ ሩጫዎች ለሃገር የማይበጁ መጥፎ ምግባራት በስፋት እየተፈጸሙ ነው::

ወያኔ የሚያራምደው የጥላቻ ፖለቲካ በጋራ ህዝቦች ለሃገራቸው በየመስኩ አስታውጾ እንዳያደርጉ በሃገራቸው ጉዳይ እንዳይሳተፉ እያደረገ ሲሆን ዲያስፖራው በተቃራኒ የሚያራምደው የጥላቻ ፖለቲካ ቁም ነገር አላባ ትግሎችን በመፍጠር ለወያኔ የስልጣን እድሜ ማስረዘሚያ በሩን ከፍቶለታል:: ዲያስፖራው የእርስ በእርስ መኮራኮም የበዛበት ፖለቲካ የሚያራምድ እና ዘላለሙን የአምባገነኖችን የማውደም ትግል ሳይሆን የወያኔን ጥላቻ የሚሰብክ አንዱ ከፍ ብሎ ሲያይ እዛው የፖለቲካ ጥጉ ላይ ጎትቶ ገደል ለመክተት የሚራወጥ ለሃገር የማይበጁ በጥላቻ የተሞሉ ስብከቶችን የሚያበዛ ትግሉን ያደነዘዘ የህዝብ እንቅፋት ነው::

ዲያስፖራው የሞላበት የጥላቻ ፖለቲካ ማስወገድ ከትግሉ በፊት ቅድሚያ ተግባሩ ነው:: አብዛኛው ዲያስፖራ በየስብሰባው እንደምናየው ሊያጨበጭብ የሚመጣው በወያኔ ላይ ያለውን የጥላቻ ፖለቲካ ተመርኩዞ እንጂ በትግል ስልቱ ላይ ያለውን ግንዛቤ ይዞ ነው:: አጨብጭቦ ዶላሩን አፍሶ የመኖሪያ ፍቃዱን የሚያድስበት የትብብር ደብዳቤ ተከብሎ ከዛ ሃገር የራሷ ጉዳይ:: ጠንከር ያለ ትግሉን የሚያጧጡፍ ሃተታ የማይዋጥላቸው ጋዜጠኞችም አንደኛው የትግሉ እሾህ ናቸው::በፖለቲካ ሽፋን ሃገር እና ህዝብ ይበዘበዛሉ ዲያስፖራው በቅንጦት ይኖራል::ይህ የጥላቻ ፖለቲካ የወለደው ጎል ነው:: ዲያስፖራው ለሃገር የሚበጅ እንቅስቃሴ የሚያደርግበትን ጊዜ እንናፍቃለን::

የወያኔ አገዛዝ እንደ እሳት የፈጀን ዜጎች የዲያስፖራው የተልፈሰፈሰ ትግል ደሞ እያንገበገን ይገኛል::ስለዚህ የህ ለሃገር የማይበጅ የጥላቻ ፖለቲካ ተወግዶ በጋራ ሃገር ከአምባገነኑ የወያኔ አገዛ የምትላቀቅበትን የጋራ ስልት መንደፍ ተገቢ ነው::

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 10 years ago on December 24, 2013
  • By:
  • Last Modified: December 24, 2013 @ 9:49 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar