www.maledatimes.com ባህር ዳር የብአዴን አመራሮች አዲስ አበባ ላይ የአማራ ብሄር የጦር መኮንኖች የስብሰባ ውጥረት - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ባህር ዳር የብአዴን አመራሮች አዲስ አበባ ላይ የአማራ ብሄር የጦር መኮንኖች የስብሰባ ውጥረት

By   /   February 26, 2014  /   Comments Off on ባህር ዳር የብአዴን አመራሮች አዲስ አበባ ላይ የአማራ ብሄር የጦር መኮንኖች የስብሰባ ውጥረት

    Print       Email
0 0
Read Time:10 Minute, 22 Second

ባህር ዳር እና አዲስ አበባ የከተመውን ሕወሓት መራሹ የብአዴን ስብሰባ ውጥረት ነግሶበታል።በቅርቡ ከፍተኛ የብኣዲን አመራሮች የፖለቲካ ጉዳዮች ሰለባ እንደሚሆኑ ተጠቁሟል::
ምንሊክ ሳልሳዊ:- የአቶ አለምነህ መኮንን ንግግር አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው ብኣዴን ለሕወሓት ግን አዳዲስ ታማኝ አሽከሮችን ለመሾም በሩን ወለል አድርጎ ከፍቶላታል::ከአዲስ አበባ እና ከባህር ዳር የሚወጡ ዘገባዎች እንደሚያመላክቱት የብኣዲን አመራሮች የፖለቲካ ጉዳዮች ሰለባ እንደሚሆኑ እና እነሱንም በአዳዲስ የሕወሓት ታማኞች ለመተካት መታሰቡን ተጠቁሟል:: የአቶ አለምነህን መኮንን ንግግርን ተከትሎ እና የተቃዋሚዎችን እንቅስቃሴና ጫና አያይዞ እንዲሁም ስለ ሙስና እና የፖለቲክ መዳከም ያነሳው የብኣዴን ስብሰባ በከፍተኛ መፈራራት እና የራስን መብት እስከመጠራጠር በሚያደርስ መልኩ እንደተካሄደ ተሰምቷል::

ውስጣዊ የፖለቲካ አፈና እንዳለ የጠቆመው ይህ የብኣዴን ስብሰባ እንዲሁም በከፍተኛ ፍራቻ እና ውጥረት የተደረገ ሲሆን የአለመተማመን ስሜቶች የመጠራጠር ሁኔታዎች እንደነበሩበት ከአመራሮቹ የመጣ መረጃ ይጠቁማል::በስፋት ሂስ እና ግለሂስ ይሰጥበታል ቢባልም ከዚህ ቀደም አቶ መላኩ እንዳሉት የሕወሓት ስውር እጆች እንዳይዘረጉ የሚል ፍራቻ በአመራሮቹ መካከል አለመተማመን ነግሶ ታይቷል::በአቶ አለምነህ ንግግር ዙሪያ ሕወሓት የራሱን እርምጃ ካልወሰደ አመራሮች በዚህ ጉዳይ ላይ ቢናገሩ ሁኔታዎች ተዘናግተው ወደ ሙስና ተለውጠው ወደ ፖለቲካዊ አፈና ስለሚያመሩ መጠንቀቅ ይበጃል የሚሉ የውስጥ አስተያየቶች በግል እንደነበሩ በምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮች ተጠቁሟል::

በአመራሮቹ መካከል ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ከታች ካድሬዎች የተሰበሰቡ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ዙሪያ ውይይት መደረጉን ተጠቁሟል::ከአቶ አለምነህ ንግግር ጀምሮ እስከ የፖለቲካ የበላይነት ….አስተያየቶች እና ጥያቄዎች ተጠይቀዋል:: የድርጅታችን አሰራር ኢዲሞክራሲያዊ ነው በውጪ የሚሰበከው ፕሮፓጋንዳ እና በገህድ የምንየው የተለይየ ነው:: የአቶ አለምነህ ንግግር የኢሕኣዴግ የበላይ ሹማምንቶች ለአማራው ብሄር ያላቸው ጥላቻ ውጤት ነው:: ብኣዼን ከሕወሓት እኩል ታግሏል ማንም ከማንም የነሰ መስዋትነት አልነበረውም ሁሉም ለነጻነት በሚል እኩል መስእዋት ነው የሆነው ቁልፍ የበላይነት ያለው በአንድ ብሄር ስር ነው አማራ ላይ ጫናው በርትቷል የሚሉ እና ተመሳሳይ ጥያቄዎች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን አቶ አለምነህ የተናገሩት ንግግርን ተከትሎ በብኣዴን አመራሮች እና ካድሬዎች መካከል ከፍተኛ የጥርስ መነካከስ ብሶበት የታየ ስብሰባ ነበር::ድርጅቱን የማይፈልጉ አባላት ራሳቸውን ሊይሰንብቱ ይችላሉ ሁኔታዎችን በሂደት እንፈታዋለን ሲሉ አቶ በረከት ተደምጠዋል::ስብሰባው የቀጠለ ሲሆን አስተይየቶች እና ጠንካራ ውይይቶች በቀጣይነት ይካሄዳሉ መፍራቱ እና መጠራጠሩ ለማቆም እንሞክራለን ሲሉ መረጃውን የሰጡ አባላት ተናግረዋል::

ከአቶ አለምነህ ጉዳይ ጎን ለጎን በጥብቅ የቀረበው ጉዳይ እና ምናልባት የብኣዴኝ መኮንኖች አቀረቡት የተባለው ተብሎ የሚጠረጠረው የብኣዴን አባላት በሙሰኞች ላይ የተጀመረውን ዘመቻ ተከትሎ በወታደራዊው ክፍል ፓርቲን እና መንግስትን ደንብን እና ህግን መደበቂያ በማድረግ ከፍተኛ ህገወጥነት እና ሙሰኝነት ይፈጸማል የሚል አቤቱታ ለድርጅታቸው ጥቆማ ቢያቀርቡን ተሰሚነት ሊያገኙ አለመቻላቸው እያበሳጫቸው መሆኑን ገልጸዋል:: የሙስናውን ክፍል በግንባር ቀደምትነት የሚመሩት የሕወሓት ጄኔራሎች ናቸው ስለዚህ በእነሱ ላይ ምርመራ ሰፋ ያለ ምርመራ ይደረግ የሚሉ ጥቆማዎች አበርትተን ብናቀርብም ምንም አይነት መልስ ልናገኝ አልቻልንም ይልቅ የሕወሓት ስውር እጆች የፖለቲካ ባላንጣዎቻቸውን በማፈን ላይ መሆናቸውን እና በቅርቡም ከፍተኛ የብኣዴን አመራሮች ወደ ፍርድ ቤት በሙሰኝነት ስም እንደሚቀርቡ ተናግረዋል::ይህ በእንዲህ እንዳለም አስቸኳይ ስብሰባ በባህር ዳር ሲጠራ በአዲስ አበባ ደግሞ የብኣዼን (አማራ)የጦር መኮንኖችን የሰበሰበ እና ለመጪው ግምገማ መንገድ ይጠርጋል የሚል ምስጢርዊ ግምገም እንደተካሄደ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ጠቁመዋል::ይህ የአማራ መኮንኖችን ብቻ ለይቶ የሰበሰበው ጉዳይ በብኣዴን ውስጥ የተፈጠረን አጣብቂኝ ያስደነገጣቸው እና የአማራው የጦር መኮንኖች ውስጥዊ ችግሮች እንዳይፈጥሩ ለማስፈራራት እና ሽብር ለመፍጠር እርስ በእርስ እንዳይተማመኑ ለማድረግ የታቀደ ሴራ ነው ሲሉ መረጃውን ያቀበሉ መኮንኖች ተደምጠውል:: በቡድን በቡድን ተከፋፍለን የምንወያይበት ጉዳይ ይኖራል የተባለ ቢሆንም ስብሰባው እንደጀመረ በአማራው መኮንኖች ላይ ጫና የሚፈጥሩ እና የሚያሸብሩ መልእክቶች ተደምጠዋል:: በተለያዩ ምክንያቶች ሰራዊቱን እንድትለቁ ማድረግ ይቻላል እስከማለት የደረሰ ዛቻ እንደተደሰኮረ ተመልክቷል::የመከላከያ ሰርዊት ውስጥ ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ዝርዝሩን እመለስበታለሁ ::ምንሊክ ሳልሳዊ

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar