www.maledatimes.com በጊምቢ (ወለጋ) በሚኖሩ ዐማሮች ላይ ስለተፈጸመው ጭፍጨፋ የመኢአድ መግለጫ፦ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

በጊምቢ (ወለጋ) በሚኖሩ ዐማሮች ላይ ስለተፈጸመው ጭፍጨፋ የመኢአድ መግለጫ፦

By   /   May 22, 2014  /   Comments Off on በጊምቢ (ወለጋ) በሚኖሩ ዐማሮች ላይ ስለተፈጸመው ጭፍጨፋ የመኢአድ መግለጫ፦

    Print       Email
0 0
Read Time:11 Minute, 25 Second

ተስፋሁን አለምነህ መኢአድ

ቀን 09/09/2006 ዓ.ም

የጊምቢ ከተማ ከአዲስ አበባ 476 ኪሎ ሜትር ርቀት ላየ ትገኛለች፡፡ በዚህች ከተማ ውስጥ የሁሉም ብሔረሰቦች በአንድ ላይ የሚኖሩ ሲሆን አኗኗራቸውም ያለምንመ ችግር ነበር፡፡ ይሁን እንጂአማሮችን እየለዩ እንዲያስወጡ በተለቀቀ ወረቀት መሠረት የኦህዲድ ካድሪኦሮሞዎች በአማሮች ላይ አመጻቸውንና ድብደባቸውን ሚያዚየ 28 ቀን 2006 ዓ.ም ልክ ከጠዋቱ በ4፡30 ላይ ጀመሩ፡፡ግጭቱም እስከቀኑ 9፡00 ሠዓት ድረስ ቀጥሎ ዋለ፡፡ ቤት ማቃጠሉና ንብረት ማወደሙም እንዲሁ ሆኖ ሰነበተ፡፡
ግጭቱ ከተነሳ በ3ኛው ቀን አፈጉባዔ አባዱላ ገመዳ ወደ ጊምቢ በማቅናት ከኦሮምኛ ተናጋሪዎች ጋር ብቻ ስፊ ውይይት አድርገው ተመልሰዋል፡፡ እንደእውነቱ ከሆነ ልጆቻቸው የተገደሉባቸውንናቤት ንብረታቸው የወደመባቸውን ዜጐች አነ…ጋግረው ቢሆን ኖሮ ምንኛ መልካም በሆነ ነበር፡፡
ከፖሊስ በተገኘው መረጃ መሠረት የሰጡት መመሪያ 1/09/2006 የአማራ ተወላጆች መውጣት እንዳይችሉ የፀጥታ ኃይሉ በሩን መዝጋት ጉዳዩም በእርቅ መፍታት አለበት የሚል ነበር፡፡ በተሰጠውመመሪያ መሠረትም የፀጥታ ኃይሉ በሩን ዘግቶ እያለ ከ02/09/06 ጀምሮ ዘረኞችና ጐጠኞች ባንጋ፣ ገጀራና አካፋ በማንሳት አማሮችን በመዝረፍ፣ቤታቸውን ማቃጠልና መግደል ጀመሩ፡፡ አቶፍሬው አያሌው የተባሉና ትውልዳቸው ደቡብ ጐንደር የሆነ የቤተሰብ ኃላፊ በገጀራና በአካፋ ተገድለው እጅና እግራቸውን ቆራርጠው ወደ ላይ አንጠልጥሎ በመያዝ ሲጨፍሩ ውለዋለየሚቀብራቸው አካልም ጠፍቶ ለሦስት ቀናት ቆይቷል፡፡
ወ/ሮ አበባ ጌቱ የተባሉና ጠላ በመጥመቅ ይተዳደሩ የነበሩ ሴት በአካፋ ጭንቅላታቸው ላየ በመመታት ወድቀው ደም እየፈሰሳቸው የነበሯቸው ሁለት በጐች የኢህዲድ ካድሪዎች ጠብሰው ሲበሉነበር ከዚህ በተጨማሪም፡-
1ኛ. ወደ አቶ አጥናፍ ምህረቱ ፎቅ አመሩ፤ የፎቁም ደረጃ G+3 ሲሆን ሕንጻው የንግድ ቤት ነው፡፡ የሚሰጧቸው አገልግሎቶች ሸቀጣሸቀጥ፣ ዱቄት፣ የምግብ ዘይት ወዘተ ሲሆን በውስጡ የያዛቸውሠራተኞች ቁጥርም 32 የቀን ሠራተኛ 14 የውስጥ ቋሚ ሰራተኛ ነበሩ፡፡ ይህ ሁሉ የሚተዳደርበትና ለክልሉ መንግሥት ከ3 ሚሊየን ብር በላይ ግብር ከፋይ እንደነበሩ ማወቅ ተችሏል፡፡ ለሀገርናለህዝብ አስተዋጽአ እያደረገ ያለ ድርጅት በብሔርተኛች ሙሉ በሙሉ ወድሟል፣ ጣራው ተቃጥሏል፡፡ በወቅቱ በእቃ ላይ የነበረው ከ10 ሚሊየን ብር በላይ እንደነበረ ወንድማቸው ነኝ ያሉኝወጣት ደሳለኝ አጫውተውናል፡፡ እኚህ ግለሰብ በድምሩ የወደመባቸው ንብረት G+3 ሕንጻ ሁለት ፎቆች እና አንድ ህንፃ መኖሪያ ቤት እንደወደመባቸው ተረጋግጧል፡፡
2ኛ. አቶ ዘሪሁን ካሴ በተመሳሳይ G+3 የወደመባቸው ሲሆን ሠራተኞችም እንደዚሁ ተበትነዋል፡፡ ድርጅቱ ይሰጣቸው የነበረው አገልግሎት የምግብ ዘይት፣ ዱቄት፣ አከፋፋይ ሲሆን ከነሙሉንብረቱ ወድሟል፡፡ ከዚህ በላይ ለአብነት ተጠቀሱ እንጂ በአጠቃላይ በሰውና በንብረት ላይ የደረሰውን ጉዳት እንደሚከተለው እንገልፃለን፡፡
1. በአሰቃቂ ግድያ የተገደሉ አቶ ፍሬው አያሌው
2. ከባድ የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው 13 ሰዎች
3. የተፈናቀሉ ወይም ቤታቸው የወደመባቸው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች 2,100.00 ሲሆን ከተፈናቀሉት ወገኖች መካከል በ60% ሴቶችና ህፃናት፣ መንቀሳቀስ የሚችሉና የማይችሉ አረጋውያን10% ሲሆኑ የተቀሩት ወንድ ወጣትና ጎልማሳዎች ናቸው፡፡
4. አሁን ያሉበት ቦታ ወይም ተፈናቃይ የሚገኙበት ቦታ 03 ቀበሌ አዳራሽ ሲሆን አዳራሹ ለጤና አያያዝም ሆነ አጠባበቅ ለምግብ አመጋገብ ምቹ ያልሆነ መፀዳጃ ቤት ለመጠቀም ከ3 ሰአት በላይየሚሰለፉበት ነው፡፡
5. የተፈናቀሉ ሰዎችን በየቦታቸው ለመመለስ ምንም አይነት ጥረት አልተደረገም እንዲያውም በራሳቸው ወጪ እንኳን ወደ ሌላ ቦታ እንዳይሄዱ በፀጥታ ሀይል ታፍነው ያለበት ሁኔታ ነዉያለዉ፡፡፡፡
6. የወደመ ንበረት በድምር 200 ሚሊየን ብር የተገመተ ሲሆን፤ እሱም በቦታው ያሉ የመንግሥት ኃላፊዎች እንዳመኑት ነው፡፡
7. ሙሉ በሙሉ በአሳት የወደሙ ቤቶች ብዛት 32
8. በርና መስኮታቸው የተሰባበሩ ቤቶች ብዛት 162 ነዉ፡፡
በቀን 07/09/2006 የደረሰ አደጋ
መኪኖች ታግተው ውለዋል፤ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት እስከ 11፡00 ሰዓት ሁሉም ሰዉ ታግቶ ነበር፡፡፤ በእለቱ በዚያው በጊምቢ ከተማ የመጀመሪያ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተነሳ ግጭት አንድ ተማሪተጎድቶ ሆስፒታል ገብቷል፡፡ በተያያዘ ሁኔታ በ06/09/2006 በነቀምት ዩኒቨርስቲ በተፈጠረ ግጭት የፀጥታ ኃይል በወሰደው እርምጃ 7 ተማሪዎች ውድ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ በአጠቃላይኢትዮጵያ መሪ የሌላት ሀገር፣ አገር የሌላቸው መሪዎች ሆነዋል፡፡
አንዲት ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 10 years ago on May 22, 2014
  • By:
  • Last Modified: May 22, 2014 @ 10:24 am
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar