www.maledatimes.com ህወሓቶች በከፍተኛ ደረጃ የኮሩበት ቀን ( በረከት ስምኦን )by tesfaye g/abe - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ህወሓቶች በከፍተኛ ደረጃ የኮሩበት ቀን ( በረከት ስምኦን )by tesfaye g/abe

By   /   September 21, 2012  /   2 Comments

    Print       Email
0 0
Read Time:7 Minute, 4 Second

“ህወሓት በአፄ ምኒልክና እና በደርግእንዲሁም በአፄ ኃይለስላሴ የነበረውን ሥርዓትአምርሮ ሲታገል የቆየው የህወሓት ስርወመንግሰትን ለመፍጠር አይደለም። ህወሓትየታገለው ዴሞክራሲያዊት የሆነች ኢትዮጵያንለመፍጠር ነው። ያንን ሁሉ መስዋዕትነትየከፈለውም ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያንለመፍጠር ነው። ስለዚህ ህወሓት የታገለው ምርጫ በዴሞክራሲ አኳን የሚካሄድበት፣ሀገሪቱ መሪዎቿን በነፃ የመትመርጥበት ሥርዓት እንዲገነባ ነው።” ( በረከት ስምኦን )ስለሆነም የሰሞኑ የኢህአዴግ ምርጫ የህወሓት የትግል ውጤት ነው። የትግራይ ሕዝብየትግል ውጤት ነው። የተከፈለው መስዋዕትነት መና እንዳልቀረ የሚያሳይ ነው። እውነትለመናገር ህወሓቶች በከፍተኛ ደረጃ የኮሩበት ቀን ቢኖር አሁን ነው።

ለእኛ ለኢህአዴጎች ይሄ የስልጣን ክፍፍል ምርጫና የመሳሰሉት ነገሮች እጅግበጣም ትንሹ አጀንዳችን ሆኖ ነው የከረመው። ይሄ ጉዳይ ትልቅ አጀንዳቸው የሆነናእያንዳንዷን ድርጊት ከምርጫው ጋር እያያያዙ ሲያስሩና ሲቀጥሉ የሚውሉ ሰዎችአሉ።አቶ ኃይለማርያም ከዚህ ስለሆነ ወደዚያ ይሄዳል። አቶ ደመቀ ከዚህ ስለሆኑወደዚህ ይሄዳሉ የሚሉ ወሬዎች መበርከታቸውን እንገነዘባለን። ያም ሆኖ አቶ መለስን’ኮየጋምቤላ ሕዝቦች፣ የደቡብ ሕዝቦች፣ የትግራይ ሕዝብ፣ የኦሮሞ ሕዝብ፣ የአማራ ሕዝብየሌሎችም ኢትዮጵያ ሕዝቦች አልፎ አፍሪካውያን ሳይቀሩ የእኛ መሪ ናቸው ብሎ ነውየተቀበላቸው። ስለዚህ ይህ ሕዝብ የሚፈልገው የመጣህበትን መሠረት አይደለም፣የመጣህበትን ብሔር አይደለም። የምትሰራለትን ስራ ነው። ይህ ነገር ያልገባቸውፖለቲከኞችና አዋቂ ነን የሚሉ ሰዎች ካሉ ችግሩ የእነሱ ነው። ኢህአዴግ እንደሆነ አቶኃይለማርያም ይሁን፣ አቶ ደመቀ፣ አቶ አዲሱ፣ አቶ አባዱላ ገመዳ ወዘተ አንድን ብሔርየሚወክሉ ሰዎች አይደሉም። በአመራር ቦታ የሚቀመጡ ሰዎች በሙሉ በስራ ክፍፍልአንድ ብሔር ላይ እንመደብ እንችላለን እንጂ አንድን ብሔር ብቻ የምንወክል ሰዎችአይደለንም። የመላው ኢትዮጵያውያንን ሕዝቦች፣ ሁሉንም ሃይማኖቶች፣ ሁሉንምብሔሮች፣ ሁሉንም ጾታዎች፣ ሁሉንም የዕድሜ ክልል በአጠቃላይ አብዛኛውን ሕዝብእንወክላለን ነው የምንለው።
በዚህ ረገድ አዲስ ነገር ፍለጋ የምንሄድበት ነገር የለንም። ባለፉት ሃያ አመታትእንደ ኢህአዴጎች በርካታ ግፊቶችን ስንቋቋም ቆይተናል። ከዚህም በኋላ አዲስ የሚመጣተፅዕኖ የለም። ካለም የእነሱንም ተፅዕኖ ለመቋቋም አዲስ የምንዘይደው መላ የለም።በአቶ መለስ ዘመን የነበረውን ሁሉንም ነገር የማስቀጠል ጉዳይ ነው። ልምዱንአግኝተናል። ዛሬ ኢትዮጵያ ማንም መጥቶ እጁዋን የሚጠመዝዝበት ደረጃ ላይአይደለችም። በጣም ረጅም ርቀት ሄዳለች። በ1983 እና በ1984 ዓ.ም ያልተንበረከከሀገርና መንግስት ዛሬ ይንበረከካል ብሎ የሚጠብቅ አካል ካለ ይሄንን ሀገርና የህዝቡንቁርጠኝነት ያልተገነዘበ ብለን ነው የምንወስደው። (በረከት ስምኦን)
Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 12 years ago on September 21, 2012
  • By:
  • Last Modified: September 21, 2012 @ 5:39 am
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%

2 thoughts on “ህወሓቶች በከፍተኛ ደረጃ የኮሩበት ቀን ( በረከት ስምኦን )by tesfaye g/abe

  1. what are you talking about? nothing is expected for ethiopian people from you. i thought nobody read you comment.

Comments are closed.

<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar