www.maledatimes.com መንገዶች ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበረ ግለሰብ በተከሰሰበት የሙስና ወንጀል በአምስት ዓመት ከስድስት ወር እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ ውሳኔ ሰጠ። - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

መንገዶች ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበረ ግለሰብ በተከሰሰበት የሙስና ወንጀል በአምስት ዓመት ከስድስት ወር እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ ውሳኔ ሰጠ።

By   /   November 22, 2018  /   Comments Off on መንገዶች ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበረ ግለሰብ በተከሰሰበት የሙስና ወንጀል በአምስት ዓመት ከስድስት ወር እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ ውሳኔ ሰጠ።

    Print       Email
0 0
Read Time:47 Second

ቤንሻንጉል ጉምዝ‼️

  1. የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የክልሉ የገጠር መንገዶች ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበረ ግለሰብ በተከሰሰበት የሙስና ወንጀል በአምስት ዓመት ከስድስት ወር እስራትና በገንዘብ #እንዲቀጣ ውሳኔ ሰጠ።p

ፍርድ ቤቱ ዛሬ ባዋለው ችሎት የቅጣት ውሳኔውን ያሳለፈው የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ በነበረው አቶ መልካሙ ታደሰ ላይ ነው።

ግለሰቡ ለመንገድ ሥራ የሚውሉ መሳሪያዎች ግዢ ለመፈፀም በወጣ ጨረታ የግዢ ስርዓቱን ባለመከተል ከ2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ የህዝብና የመንግስት ሃብት እንዲባክን በማድረጉ ውሳኔው እንደተላለፈበት በችሎቱ ተመልከቷል።

የተሰጠውን የመንግስት ኃላፊነት አለአግባብ በመጠቀም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከ2008 እስከ 2009 ዓ.ም የተለያዩ መስሪያዎችን ግዢ ለመፈፀም ባወጣው ጨረታ አሸናፊው ድርጅት ላሸነፈበት የውል ማስከበሪያ ሳያቀርብ ውል እንዲገባ በማድረግ የውሉን 30 በመቶ ቅድመክፍያ እንዲፈፀም ትዕዛዝ መስጠቱ ተጠቅሷል።

በጨረታው አሸናፊ የሆነው ድርጅት ቅድመ ክፍያ ተቀብሎ በገባው ውል መሰረት መሳሪያዎቹን ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሳያቀርብ መቅረቱም በችሎቱ ተመልክቷል፡፡

ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተው የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ከዋለበት ጊዜ አንስቶ በአምስት ዓመት ከስድስት ወር ጽኑ እስራትና በ20 ሺህ ብር ገንዘብ እንዲቀጣ ውሳኔ ሰጥቷል።

ምንጭ፦ ኢዜአ

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on November 22, 2018
  • By:
  • Last Modified: November 22, 2018 @ 11:11 am
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar