www.maledatimes.com 6 የሱማሌ ክልል ከፍተኛ ኃላፊዎች ከሥልጣናቸው ተነሱ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

6 የሱማሌ ክልል ከፍተኛ ኃላፊዎች ከሥልጣናቸው ተነሱ

By   /   January 29, 2019  /   Comments Off on 6 የሱማሌ ክልል ከፍተኛ ኃላፊዎች ከሥልጣናቸው ተነሱ

    Print       Email
0 0
Read Time:39 Second

ረቡዕ፣ ጥር 15 የሱማሌ ክልል መንግሥት ካቢኔ ባደረገው ስብሰባ ስድስት የክልሉን ከፍተኛ አመራሮች ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ወስኗል።
ከኃላፊነት ከተነሱት ውስጥ የክልሉ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ እና የምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አማካሪ ይገኙበታል።

የኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊውም ምክትላቸው በነበሩት አብዱላሂ መሐመድ ተተክተዋል።

‹‹ለአመራሮቹ ከስልጣን መነሳት ምክንያት የሆነው በክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፋ ዑመር መሐመድ እና በአህመድ ሽዴ ሊቀ መንበርነት በሚመራው የኢትዮጵያ ሶማሌ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሕሶዴፓ) አመራሮች መካከል ኹለት ቡድን መመስረቱ ነው፤ በቡድኑ መካከልም የሥልጣን ሽኩቻ ተፈጥሯል›› የሚሉ መረጃዎች በማኅበራዊ ትስስር ገጾች እየተዘዋወሩ ነው።

ይሁንና ‹‹የክልሉን ገዢ ፓርቲ ኢሶሕዴፓንና የክልሉን መንግሥት አስመልክቶ በማኅበራዊ ድረ ገጾች የሚናፈሰው ወሬ መሠረተ ቢስ›› ነው ሲሉ አዲሱ ቃል አቀባይ አብዱላሂ መሐመድ ለኢዜአ በሰጡት ምላሽ አጣጥለዋል።

ኢሶሕዴፓ በነሐሴ 2010 በጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ባደረገው ግምገማ፣ ሦስት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴና አምስት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ማንሳቱ ይታወሳል።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on January 29, 2019
  • By:
  • Last Modified: January 29, 2019 @ 3:14 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar