www.maledatimes.com በቃሊቲ እስርቤት በታራሚ እስረኞች ላይ ፖሊስ ጥቃት ፈጸመ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

በቃሊቲ እስርቤት በታራሚ እስረኞች ላይ ፖሊስ ጥቃት ፈጸመ

By   /   April 16, 2019  /   Comments Off on በቃሊቲ እስርቤት በታራሚ እስረኞች ላይ ፖሊስ ጥቃት ፈጸመ

    Print       Email
0 0
Read Time:51 Second

በቃሊቲ ፍረኞች ላይ ፖሊስ ግቢውን ሰብሮ በመግባት ጥቃት መፈጸሙን ተገለጸ ።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ከኦሮሚያ ፖሊስ ጋር በመተባበር የማረሚያ ቤቱን ህግ እና ደንብ በመጣስ ከማረሚያ ቤቱ አዛዥ ጀርባ በተደረገ ደባ ወጣት ታራሚ እስረኞችን ስርአተ ጸሎት በሚያደርጉበት መስጅድ ውስጥ ዘልቆ በመግባት በንጹሃን ዜጎች ላይ ድብደባ ማድረጋቸው ተገልጿል ።

መነሻው ምንም ያልታወቀው እና ያልተጣራው ይሄው ጥቃት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ሊያስጠይቀው ይገባል በህግ ፊት ሊቀርብ እና አቤቱታውን ማሰማት አለበት ሲሉ የፍርደኞች ቤተሰቦች ገልጠዋል።

ብዙ እስረኞች የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው የተጠቆመ ሲሆን ሁለት ሰዎች መሞታቸውንም እስከአሁን የደረሰን መረጃ ይጠቁማል ።

ባለፈው ወር እስረኞች እርስ በእርስ በመደባደብ ብዛት ያላቸው እስረኞች መሞታቸው የሚታወቅ ሲሆን እስረኞችንም ሆነ በማረሚያ ቤት አስተዳደር ይህ ጉዳይ እንዳይታወቅ የሸፋፈኑት እና መገናኛ ብዙሃኖች እንዳይዘግቡት ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ መክረሙን ከውስጥ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

Image may contain: 1 person, standing and beard

በአዲስ አበባ ኮሚሽን ስር የሚተዳደረው የቃሊቲ እስርቤት ብዙሃኖችን በማሰቃየት እና ለሞት በመዳረግ ከሚታወቁት ትልልቅ አሰቃቂ እስርቤቶች ውስጥ ግንባር ቀደሙን እንደሚወስድ የደረሰን መረጃ ያጠናክራል።

በተለይም በዞን አንድ እና ሁለት የሞት ፍርደኞች እና የእድሜ ልክ ፍርደኞች ላይ የሚበዛው ሰቆቃ ሰፊ እንደሆነ እና በፖሊሶች ድብደባ ብዙዎቹ ህይወታቸው እንደሚያልፍ እስረኞች አዲስ አበባ ለሚገኘው ለማለዳ ታይምስ ዘጋቢ አሳስበዋል።

Image may contain: 3 people, people standing

Image may contain: 1 person

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 5 years ago on April 16, 2019
  • By:
  • Last Modified: April 16, 2019 @ 12:24 pm
  • Filed Under: Ethiopia

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar