www.maledatimes.com የፍርድ ቤት ውሎ ጋዜጠኛ ተመስገን ደስአለኝ ለሃምሌ ሁለት ተቀጠረ - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

የፍርድ ቤት ውሎ ጋዜጠኛ ተመስገን ደስአለኝ ለሃምሌ ሁለት ተቀጠረ

By   /   May 30, 2013  /   Comments Off on የፍርድ ቤት ውሎ ጋዜጠኛ ተመስገን ደስአለኝ ለሃምሌ ሁለት ተቀጠረ

    Print       Email
0 0
Read Time:7 Minute, 16 Second

ፍርድ ቤቱ የተከሳሽን  ቃል ሲሰማ እና ጠበቆች ስለምስክሮቹ መግለጫ ሲሰጡ ሰዓቱ ስላለቀ ሃምሌ 2 የምስክሮቹን የምስክርነት ቃል ለመስማት ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ የተመስገን ጠበቃ ምስክሮቹ በምን ጉዳይ ላይ ምስክርነታቸውን እንደሚሰጡ ከተናገረ በኋላ አቃቢ ህግ የሁለቱ መስካሪዎች እንዳይመሰክሩ በምክንያት አስደግፈው ተቃውመው ነበር::  በዚህም መሰረት አንደኛው ምስክር ዶ/ር ያሬድ ከህገ መንግስቱ እና ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ሃሳብን የመግለፅ መብቶች ከሚደነግጉ ህጎች አንፃር ተመስገን የተከሰሰባቸው ፅሁፎች ከህግ ውጪ እንዳልሆኑ ያስረዳሉ ::  ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም ደሞ ኢሰመጉ ይሰሩባቸው በነበሩበት ወቅት በኢሰመጉ ሪፖርት የቀረቡ በኢትዮጵያ መንግስት ስለተጣሱ ሰብአዊ መብቶች ያቀርባሉ::   አቶ እንዳልካቸው ሃ/ሚካኤል ክስ የቀረበባቸውን ፅሁፎች ከጋዜጠኝነት ስነምግባር እና አሰራር ከሙያ አንፃር እንዴት መታየት እንዳለበት ያቀርባሉ:: አቃቤ ህጎች የሁለቱ ምስክርነት ቃል እንዳይሰማ ብለው ተቃሟቸውን አቅርበው ነበር በ1ኛ እና 2ኛ ምስክሮች ላይ::394711_184013551696255_1365830121_n

ጠበቆቹ ስለምስክሮቹ መግለጫ ካቀረቡ በኋላ አቃቤ ህጎቹ በ1ኛ እና 2ኛ ምስክር ላይ ተቃሞ እንዳላቸው ተቃሟቸውን አቀረቡ:: 1ኛ ምስክር ዶ/ር ያሬድ የህግ ባለሙያ ቢሆኑም ህገመንግስቱን የመተርጎም ስልጣን የላቸውም :  ህገመንግስቱን የመተርጎም ስልጣን ያለው የፌዴሬሽን ም/ቤት ብቻ ነው ስለዚ የሳቸው ምስክርነት አያስፈልግም:: 2ኛ ምስክር ፕ/ር መስፍን ኢሰመጉ ሊቀመንበር ሆነው የሰሩ ቢሆንም ከ97 በኋላ ባላቸው የፖለቲካ እንቅስቃሴ እና አቋም ገለልተኛ ሆነው መመስከራቸው ያጠራጥረናል ስለዚህ የሁለቱን ምስክር ሆኖ መቅረብ ፍ/ቤቱ ውድቅ እንዲያደርግ ጠይቀዋል::

የተከሳሽ ጠበቆችም ምላሽ ሲሰጡ : 1ኛ ምስክር ዶ/ር ያሬድ ህገመንግስቱን እንዲተረጉሙ ሳይሆን ደንበኛቸው የተከከሰሰባቸው ፅሁፎች ከህገመንግስቱ እና ኢትዬጵያ ከፈረመቻቸው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ከሚደነግጉ አለም አቀፍ ህጎች አንፃር እንዴት ትክክል እንደሆኑ ለማስረዳት መሆኑን 2ኛ ምስክር ፕ/ር መስፍን ደግሞ የሚያቀርቡት ኢሰመጉ ሲሰሩ በነበሩባቸው ጊዜያቶች ያዩትን የሰሙትንና ድርጅቱም በሪፖርቱ ያካተታቸውን ጉዳዮች እንጂ ሌላ ነገር አለመሆኑም..የገለልተኝነታቸው ጉዳይ በተመለከተ ደግሞ በህጉ ምስክሮች ገለልተኛ መሆን አለባቸው የሚል እንዳልተጠቀሰ ..አቀረቡ:: ዳኛውም ግራ ቀኙን ካዳመጡ በኋላ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላለፉ:: በአቃቤ ህግ ተቃሞ የቀረበባቸው ምስክሮች 1ኛ ምስክር ዶ/ር ያሬድ ህገመንግስቱን መተርጎም እንደማይችል ነገር ግን ከዛ ውጪ ባለው እውቀት ክስ የቀረበባቸውን ፅሁፎች ከህገመነግስቱ እና ሌሎች ህጎች አንፃር እንደማያስከስሱ ብቻ ማቅረብ እንዳለባቸው 2ኛ ፕ/ር መስፍንም ኢሰመጉ ሲሰሩ በነበሩበት ወቅት የሚያቁትን ብቻ እንዲያቀርቡ፡፡ ገለልተኛ ለተባለው…መስካሪዎች ገለልተኛ እንዲሆኑ የሚል ደንብ ስለሌለ ማንኛውም ሰው ያለምንም ልዩነት የምስክርነት ቃል መስጠት ይችላል::

በፍትሕ ጋዜጣ ላይ፣ የተዘገቡ ”የካቲት 23 2004 ዓ.ም በተሰራጨው የፍትህ ጋዜጣ ቅጽ 05 ቁጥር 177 እትም የፈራ ይመለስ በሚል” : ”በቅጽ 5 ቁጥር 179 መጋቢት 7 2004 ዓ.ም ዕትም መጅሊሱና ሲኖዶሱ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ማጥመቂያ” እና “ ሐምሌ 22 ቀን 2003 ዓ.ም የሁለተኛ ዜግነት ህይወት በኢትዮጵያ እስከመቼ?”  በሚሉ ርእሶች በወጡ መጣጥፎችን ተከትሎ ”የሕዝብን ሐሳብ ማናወጥ፣ሕዝቡን በሕገ-መንግስቱ ላይ ማነሳሳትና የመንግስትን ስም በማጥፋት” በሚሉ ሶስት ክሶች ነው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የተከሰሰው::source Dagmawi Tewoderos

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 11 years ago on May 30, 2013
  • By:
  • Last Modified: June 1, 2013 @ 4:24 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar