ሕገ መንግሥቱን እንደጣሰ እየታወቀ ሲሠራበት የነበረ ደንብ ለሕገ መንግሥት ትርጉም ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ተላከ
የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሠራተኞችን በሕግ የመዳኘት ሕገ መንግሥታዊ መብታቸውን ገፎ የነበረና ባለሥልጣኑ ከአሥር ዓመታት በላይ ሲጠቀምበትና ሲያስፈራራበት የነበረው ደንብ ቁጥር 155/2000፣ ሕገ መንግሥቱን ተቃርኖ እንዳገኘው የሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባዔ አስታወቀ፡፡ የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 37(1)፣ ‹‹ማንኛውም ሰው በፍርድ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ለፍርድ ቤት ወይም በሕግ የዳኝነት ሥልጣን ለተሰጠው አካል የማቅረብና ውሳኔ ወይም ፍርድ የማግኘት […]
Read More →ከኢትዮጵያ በዘጠኝ ዓመታት 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሸሸ ሪፖርት ተደረገ
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ሥር የሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ይፋ ያደረገው የአፍሪካ የጤና ክብካቤና የኢኮኖሚ ዕድገት ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ወደ ውጭ በሕገወጥ መንገድ እንደሸሸባት አስታውቆ፣ ይህ ገንዘብ ለጤናው ዘርፍ የምታውለውን 87 በመቶ በጀት እንደሚሸፍን አመለከተ፡፡ ማክሰኞ የካቲት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ […]
Read More →“ባለቤት ያቃለለውን አሞሌ ባለ ዕዳ አይቀበለውም” በዳንኤል ክብረት
“ትንቢተ ዳንኤል” እና የንጉሠ ነገሥቱ ሐውልት ሙኃዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት የዛሬ ሰባት ዓመት ገደማ (የካቲት 2004 ዓ.ም) “ባለቤት ያቃለለውን አሞሌ ባለ ዕዳ አይቀበለውም” በሚል ርእስ ግሩም የሆነ ጽሑፍ አስነብቦን ነበር፡፡ ለጽሑፉ ምክንያት የሆነው በአፍሪካ ኅብረት ጽ/ቤት ለክዋሜ ንክሩማህ የቆመው መታሰቢያ ሐውልት ለንጉሠ ነገሥት ኃይለ ሥላሴ ያለመቆሙ ጉዳይ ነበር፡፡ ዘንድሮ ጊዜው ሲደርስና የመታሰቢያ ሐውልት ሲቆምላቸው የተስፋው […]
Read More →የምርጫ ቦርድን ከመንግሥት ተፅዕኖ የሚያላቅቅና ገለልተኝነቱን ያስጠብቃል የተባለ ረቂቅ ሕግ ቀረበ
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለልተኛና ከመንግሥት ተፅዕኖ ተላቆ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ሆኖ በድጋሚ እንዲቋቋም ያስችላል የተባለ ረቂቅ ሕግ፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ። ምክር ቤቱ ጥር 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሄደው ልዩ ስብሰባ ረቂቅ ሕጉን የተመለከተ ሲሆን፣ በዝርዝር እንዲታይም ለሕግ ፍትሕና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል። ረቂቅ ሕጉ በቀረበበት ወቅት በማብራሪያ አስተያየታቸውን የሰጡት በምክር ቤቱ የመንግሥት ረዳት […]
Read More →ፓርላማው በአስተዳደሩ የተነጠቀውን መሬት ለማስመለስ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ድጋፍ አገኘ
በአቅራቢያው ተጨማሪ ቢሮ በ15 ሚሊዮን ብር ተከራየ በቅርቡ ለዓመታት ታጥረው የቆዩ መሬቶችን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወሰደው ዕርምጃ ሲያስመልስ አብሮ የተነጠቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የተወሰደበትን መሬት ለማስመለስ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ድጋፍ ማግኘቱ ታወቀ፡፡ ሪፖርተር ከታማኝ ምንጮች ማወቅ እንደቻለው ጥር 24 ቀን 2011 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ሪፖርት ካቀረቡ […]
Read More →በእስረኞች ላይ ሽንት በመሽናትና ጥፍር በመንቀል የተጠረጠረችው መርማሪ 11 ክሶች ተመሠረቱባት
በሽብር ወንጀል ተፈርጀው ታስረው በነበሩ የኦነግና አርበኞች ግንቦት ሰባት አባላት ላይ ሽንት በመሽናት፣ ጥፍር በመንቀልና በሌሎችም ዘግናኝ የተባሉ የወንጀል ድርጊቶች ተጠርጥራ የታሰረችው፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ የቀድሞ አባል ዋና ሳጅን እቴነሽ አረፉዓይኔ 11 ክሶች ተመሠረቱባት፡፡ ተከሳሿ በተለምዶ ማዕከላዊ ይባል የነበረውና በቅርቡ በተዘጋው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ ቡድን መሪና መርማሪ ሆና ስትሠራ፣ ካልተያዙ ግብረ […]
Read More →በአገሪቱ ‹‹የጨለማ ኢኮኖሚ›› እንቅስቃሴ መንሰራፋቱን የገቢዎች ሚኒስትሯ አመለከቱ
በፖለቲካ አለመረጋጋቱን ሳቢያ ግብር የማይከፍሉ በርካታ ግብር ከፋዮች መኖራቸው ተገልጿል ለረዥም ዓመታት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ የሕግ ማሻሻያ ሊደረግ ነው ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ ከሚደረገው ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በተቃራኒው ሰፊ የሆነ ‹‹የጨለማ ኢኮኖሚ›› እንቅስቃሴ መኖሩንና ሁሉም የመንግሥት መዋቅር ተናቦና ተቀናጅቶ መዋቅሩን ካላፈራረሰው፣ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት ከማድረስ አልፎ ፖለቲካዊ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል የገቢዎች ሚኒስትሯ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አስታወቁ፡፡ […]
Read More →የየካ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት የ18 ሚሊዮን ብር የሕንፃ ኪራይ ጥያቄ አስነሳ
በየካ ክፍለ ከተማ ሥር የሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት፣ ቀድሞ በዓመት አምስት ሚሊዮን ብር እየከፈለበት ካለው ሕንፃ በመልቀቅ በዓመት 18 ሚሊዮን ብር ወደሚከፈልበት ሕንፃ ለመዘዋወር የኪራይ ውል መፈጸሙ ጥያቄ ተነሳበት፡፡ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የቢሮው ሠራተኞች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ 22 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከኢትዮጵያ ቱሪስት ንግድ ሥራ ፊት ለፊት የሚገኘው የየካ ክፍለ ከተማ […]
Read More →‹‹ሼክ አል አሙዲ ለኢትዮጵያ ልማትና ዕድገት አለኝታ ስለነበሩ እንዲፈቱ ጥረት አድርጌያለሁ››
ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር)፣ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ባደረገው የፀረ ሙስና ዘመቻ ከአንድ ዓመት በላይ ታስረው የቆዩት ሼክ መሐመድ ሁሴን ዓሊ አል አሙዲ፣ ከእስር እንዲፈቱ የዓለም ጤና ድርጀት ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር) ሚና እንደነበራቸው ገለጹ፡፡ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ ሥልጣን ከያዙ ከሳምንት በኋላ እዚህ መጥቼ ተገናኝተን ነበር፡፡ በወቅቱ የሼክ አል አሙዲን ጉዳይ […]
Read More →የቴሌኮሙኑኬሽን መስሪያቤት በግል ሴክተር ባለሃብቶች የሚያዝበት ረቂቅ አዋጅ ቀረበ!
የቴሌኮም አገልግሎት ረቂቅ አዋጅ በሚል ስያሜ የተዘጋጀው ሰነድ ኢትዮጵያን በቴሌኮም ዘርፍ ለመሰማራት ለፈለገ የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለ ሀብት ክፍት የማድረግን የመንግስትን ፍላጎት ይፋ አድርጓል። ረቂቅ አዋጁ የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ባለፈው አመት በቴሌኮም ዘርፉ እንዲተገበር ከወሰነው ሰፋ ባለሁኔታ ዘርፉን ለገበያ ክፍት የሚያደርግ ነው። ቀድሞ ተነግሮ የነበረው መንግስት የኢትዮ ቴሌኮምን አብላጫ ድርሻ ይዞ ቀሪውን ለሀገር […]
Read More →
