www.maledatimes.com ለ አብራሪው ( በይግዛው እያሱ) - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

ለ አብራሪው ( በ ይግዛው እያሱ)

By   /   February 21, 2014  /   Comments Off on ለ አብራሪው ( በ ይግዛው እያሱ)

    Print       Email
0 0
Read Time:2 Minute, 58 Second

ቢመረው ቢከፋው ግፍ አላይም ብሎ
ጨርቄን ማቄን ሳይል ካገር ወጣ ጥሎ።
ለሙያው ሊታመን ምሎ ቢቀጠርም
ስራን በነጻነት ሊያገኘው አልቻለም።
የህዝብ ብሶት መከራ በሱ ተመስሎ
ላይመለስ ሸኘው ድምጽ አሰማ ብሎ።
ይህ የህዝብ ድምጽ ነው የአንድ አገር ዜጋ
በግፍ የሚገረፍ በወያኔ አለንጋ።
22 ዓመት ህዝብ ከህዝብ ከፋፍለው
አንዱን ባንዱ አዝምቶ አንገት የሚያስደፋው
የወያኔን መንግስት የግፍ አገዛዙን
ለዓለም ሊያሳውቅ ነው በመጥላት እራሱን።
በጣም በተሻለ መኖር እየቻለ
ለሆዱ ሳያድር ነጻነቴን ያለ
የቁርጥ ቀን ጀግና እንደ ሀይሌም የለ። (ሀይለመድህን)
የዓለም መንግስታት ይህን ይወቁልን
ለሀይለመድህን አበራ ጥሩ ፍርድ ይስጡልን።
ወያኔ እንደሚለው አሸባሪ አይደለም
ወያኔ እንደሚለው አገሩን አልከዳም
ወያኔን ግን ከድቷል ህዝብን አስቀድሞ
ራሱን ሻማ አርጎ የወገን ድምጽ ሆኖ።
ቢሞትም አይቆጭም ቢያስሩትም ይፈታል
ያጎነበሰን ህዝብ አንገት ቀና አድርጓል።
ለተበደለው ህዝብ ድምጹን አሰምቷል።
ሞት አዲስ አይደለም በኢትዮጵያ ምድር
ሁሉ ሚከፍለው ነው ለወያኔ ግብር።
የሱም ተራ ደርሶ ለእርድ ሳይዘጋጅ
በሰማይ እያለ እግዚአብሔር እረድቶት
እራሱ አመቻችቶ ዘዴ ፈጠረለት
ህዝብን አድን አለው ሂድና ጩህለት።
ቃሉን ተቀብሎ ለራስ ሳያዳላ
ጄኔቭ ገባ ሀይሌ ለመፈለግ መላ።
መላ ባንተ ይገኛል ድካምህ አይቀርም
የዓለም መንግስታት ይህን ዝም አይልም።
በቅርብ ታየዋለህ ካንተ ፍርድ ጀምሮ
የኢትዮጵያ አምላክ አይጥልህም ጥሎ።

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 10 years ago on February 21, 2014
  • By:
  • Last Modified: February 21, 2014 @ 8:16 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar