www.maledatimes.com በጎንደር ዩኒቨርስቲ ዩ-ቲዩብ እና ፌስ ቡክ ተዘጋ ;ኢንተርኔት መጠቀም በግቢው ውስጥ ተከልክሏል - MALEDA TIMES
Loading...
You are here:  Home  >  Ethiopia  >  Current Article

በጎንደር ዩኒቨርስቲ ዩ-ቲዩብ እና ፌስ ቡክ ተዘጋ ;ኢንተርኔት መጠቀም በግቢው ውስጥ ተከልክሏል

By   /   October 2, 2012  /   Comments Off on በጎንደር ዩኒቨርስቲ á‹©-ቲዩብ እና ፌስ ቡክ ተዘጋ ;ኢንተርኔት መጠቀም በግቢው ውስጥ ተከልክሏል

    Print       Email
0 0
Read Time:9 Minute, 3 Second

ባለፈው ሳምንት በጎንደር ዩኒቨርስቲ የተከናወነውን ስብሰባ አስመልክቶ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በመንግስት ሃይሎች እና በዩኒቨርሲቲ መምህራን መካከል የተካሄደው ስብሰባ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው ። “ግንቦት ሰባት እና ግንቦት ሃያ እኩል ሊታዩ ይገባል” ተባለ በሚል  ዜና መዘገባችን ይታወሳል ።ዛሬ በደረሰን መረጃ መሰረት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር በመላው የአካዳሚክ ማእከል ውስጥ የሚገኙትን የኢንተርኔት ኔትወርኮች ፌስ ቡክ እና ዩ-ቲዩብ እንዳይመለከቱ መዝጋታቸውን እየሚያመለክት የዜና ምንጫችን ጠቁሟል ።

እንደ ደረሰን መረጃ መሰረት በትምህርት ተቋም ውስጥ የተከሰተው ይኸው የኢንተርኔት መታገድ ምክንያት ባለፈው በማለዳ ታይምስ ላይ ተሰርቶ የነበረውን  ዜና አስመልክቶ አስተዳደሩ ስለተናደዱ ነው ሲሉ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚሰሩ መምህራን ለማለዳ ታይምስ ጠቁመዋል ።በግቢው ውስጥ ለምተገኙ መምህራን እና ተማሪዎች የተዘጋውን ዌብሳይት ለመክፈት ይህንን ሊንክ http://pray3.com/ በመፈለጊያ ቦታው ላይ በማስቀመጥ ፈልግ ብላችሁ ፣እንዳይዘጋባችሁ ማድረግ የምትችሉ መሆኑን የማለዳ ታይምስ ዝግጅት ክፍል ትብብሩን ያደርጋል ፣ለዚህም ሊንክ እንደ ገና ከተዘጋባችሁ ሌላ ተያያዥ ሊንኮችን በመቀያየር መክፈት የምትችሉ መሆኑን እንጠቁማለን ።

በተዘጋው የኢንተርኔት መጠቀምን አስመልክቶ ብዙዎችን ሰራተኞችን ተማሪዎችን እና ሌሎችንም የአስተዳደር አካላትን ያስቆጣ መሆኑን ሲጠቁሙ ፣በማደግ ላይ ያለ ተቋም ከሚባሉት ተርታ ሳይመደብ ትልቅ ተቋም ነው እየተባለ የሚወራውን ይህንን ተቋም የመረጃ ነጻነት እና የአገልግሎት እጥረት የተማሪውን የመማር አቅም የሚጎዳ ከመሆኑም በላይ የወደፊት እራእያቸውን የሚያቀጭጭ ነው ሲሉ መምህራኑ አስተያየታቸውን ለማለዳ ታይምስ ገልጸዋል።ይህ ደግሞ የ እኛን የመምህርነት ምግባር በትክክል እንዳንሰራ የሚያግደን እና ነጻነታችንን ጭምር የሚጋፋም ነው ብለዋል ።በተለይም የተለያዩ ምርምራዊ ስራዎችን ለመስራት እና ዋቢ መጽሃፍትን ከተለያዩ ቦታዎች በአጭር ጊዜ ለመፈለግ እና እውቀትን ለተማሪዎቻችን መመገብ የሚገባንን ሁሉ ለማድረግ ያግደናል ይህ ግን የነጻነት እና የመናገር እንደዚሁም የሰውልጅ መብትን ሁሉ የሚጋፋ ነገር ነው ሲሉ ገልጸዋል።በዚሁ ሁኔታ መምህራኖች የጋራ አቋም መግለጫ ወይንም የስራ ማቆም አድማ ለማድረግ በጥረት ላይ መሆናቸውን ምንጮቻችን ለማለዳ ታይምስ ዘግበዋል።

በሌላም መልኩ በገለጹት መረጃ መሰረት አስተዳደሩ በሙስና የተጨማለቀ እና እንዲሁም ከመለስ አስተዳደር ጋር አጣብቂኝ የነበራቸው ሰዎች ዛሬም ከአማራ ክልል መንግስት ጋር እና እንዲሁም የወያኔ ኢሃዴግ አስተዳደርን የሙጥኝ ብለው የጥቅማቸው መሳሪያ ያደርጉት መምህራን እና አስተዳደሮች የጎንደር ዩኒቨርሲትይን የልዩ ጥቅም ቤታቸው አድርገው ከመሰረቱት ቆይተዋል  ብለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአጠቃላይ ለተለያዩ ሃገራዊ ክብረ በአሎች መሰጠት የሚገባው ክብር ቀርቶ ለግንቦት ሃያ የሚሰጡት ክብር እና ዝና ከምንም በላይ ነው በ እለቱ የሚሰጣቱት መዋእለ ነዋይ እጅግ ውድ ከመሆኑም የተነሳ የዩኒቨርስቲውን በጀት የሚያራቁት እንደሆነም አክለው መምህራኑ ገልጸዋል

 

MARAKI LIBRARY

 

 

 

ማሳሰቢያ፤በዌብሳይታችን ላይ ለሚወጡ ማናቸውም ጽሁፎች ቀዳሚ የሆነ የዌብሳይታችንን አርትኦት ስራን ለማክበር ሲባል በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በማለዳ ታይምስ የመረጃ ማእከል ® ላይ ለሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የማለዳ ታይምስ የመረጃ ማእከል ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዌብሳይቱን  ጠቋሚ (አመልካች ) (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.maledatimes.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን(የማለዳ ታይምስ ህግና ደንብ በንግድ በተመዘገቡበት ሁለት አገሮች የረቀቀ ሲሆን በሁለቱም አገሮች አንድ አይነት የሆነ አሰራር ይዞ ይከተላል ።ይህንን ህግ ማንኛውም ሰው መቅዳት የማይችል መሆኑን እንገልጻለን።ንብረትነቱ እና ህገ ደንቡ የማለዳ ታይምስ ብቻ ነው!)፡፡ይህ ካልሆነ ግን በህገ ደንባችን መሰረት አስፈላጊውን የህጋዊ ጥያቄ ለማቅረብ የምንገደድ መሆኑን እንጠቁማለን::በዚህ አጋጣሚ በግለሰብ ለሚላኩ ጽሁፎች ሁሉ ተጠያቂው ስሙ የተገለጸው ግለሰብ እንጂ የማለዳ ታይምስ መረጃ ማእከል ሃላፊነቱን እንደማይወስድ እናሳስባለን ::

Happy
Happy
0 %
Sad
Sad
0 %
Excited
Excited
0 %
Sleepy
Sleepy
0 %
Angry
Angry
0 %
Surprise
Surprise
0 %
    Print       Email
  • Published: 12 years ago on October 2, 2012
  • By:
  • Last Modified: October 2, 2012 @ 5:35 pm
  • Filed Under: Ethiopia
  • Tagged With:

Average Rating

5 Star
0%
4 Star
0%
3 Star
0%
2 Star
0%
1 Star
0%
<"Without the support of our readers, the Maleda Times website would not exist in its present form">

You might also like...

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ መከላከያ ከአማራው ማህበረሰብ እና ከፋኖ ጋር ጦርነት ገጥሟል

Read More →

This site is protected by wp-copyrightpro.com

%d bloggers like this:
Skip to toolbar